የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን እንቅስቃሴ አቀላጥፏል

Jun 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን የትራፊክ ፍሰትና አጠቃላይ እንቅስቃሴ ለማቀላጠፍ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በአሶሳ ከተማ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት፤ የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማዘመን፣ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና ከተማዋን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ሳቢ ለማድረግ ታስቦ የተጀመረ ሰፊ መርሃ ግብር ነው።

በአንደኛው ዙር የተከናወኑት ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ተከትሎ፣ አሁን ላይ ትኩረቱን የንግድና ማህበራዊ አገልግሎት ማዕከላትን ማዘመን ላይ ያደረገው ሁለተኛው ዙር ስራ በስፋት እየተገነባ ይገኛል።

የሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ብቻ ሳይሆን ምቹ የእግረኛና የተሽከርካሪ መንገዶችንም በማካተት የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ይገኛል።

አስተያየታቸውን የሰጡን የከተማዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ የእግረኛ እና የተሽከርካሪ መንገዱ ተለይቶ መሰራቱ የትራፊክ ፍሰቱን በእጅጉ አቅልሎታል።


ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ማስረሻው አራጌ እንዳሉት፣ ከዚህ ቀደም የነበረው መንገድ ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ ለተሽከርካሪም ሆነ ለእግረኞች ምቹ እንዳልነበር አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅት ግን በኮሪደር ልማቱ ለሁሉም ምቹ መንገድ በመፈጠሩ፣ የትራፊክ እንቅስቃሴው መሳለጡን አቶ ማስረሻው ተናግረዋል።

ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ የሺወርቅ ንብረት፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን በሁሉም መስክ ለነዋሪዎቿ ምቹ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።


በተለይም በሁለተኛው ዙር እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት፣ በእግረኞች ላይ ይደርስ የነበረውን የትራፊክ አደጋ በመቀነስ ረገድ አይነተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

በከተማዋ የባጃጅ አሽከርካሪ የሆነው አህመድ ሰኢድ በበኩሉ የኮሪደር ልማቱ ለአሸከርካሪዎች ነፃነትን የሰጠ እና ለተሽከርካሪዎችም ምቹ መሆኑን ተናግሯል።


የኮሪደር ልማቱ ለአሸከርካሪዎች እና እግረኞች የፈጠረው ምቹ ሁኔታ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስ አንፃር ትልቅ ትርጉም አለው ያሉት ደግሞ በአሶሳ ከተማ የትራፊክ ተቆጣጣሪ ምክትል ሳጅን ኢዘዲን አልበሽር ናቸው።


የኮሪደር ልማቱ የትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን የሥራ ጫና የቀነሰ እና የተቀላጠፈ የትራፊክ እንቅሰቃሴ እንዲፈጠር አይነተኛ ሚና ያበረከተ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026