የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቀጣናዊ ደህንነትን በማረጋገጥ በትብብር ላይ የተመሰረተ የጋራ ዕድገትን ይፈጥራል

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቀጣናዊ ሰላምና ደህንነትን በማረጋገጥ በትብብር ላይ የተመሰረተ የጋራ ዕድገትን እንደሚፈጥር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና ምሁር ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት ከዓለም ጋር የምትገናኝባቸው የብዝሃ ባሕር በርና የባሕር ዳርቻ መዳረሻ ወደብ ባለቤት እንደነበረች በታሪክ ተሰንዶ ይገኛል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ላይ የተፈጸመው በደል የሚያስቆጭ ነው።

በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ማግስት የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ መነሳቱም ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የህዝብ ቁጥርና የደኅነነት ስጋቶችን መቀልበስ የሚስችል ትብብር ከማጎልበት የሚመነጭ መሆኑን ገልጸዋል።

ሀገራዊ ለውጡም ለበርካታ ዓመታት በህዝብ ልብ ተዳፍኖ የቆየውን ታሪካዊ፣ ፍትሐዊ፣ ሕጋዊና መልክዓ ምድራዊ የባህር በር ባለቤትነት ግልጸኝነት መፍጠሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሰላማዊ፣ ሕጋዊና የጋራ ተጠቃሚነት መርህን ተከትሎ መቅረቡም ዓለምአቀፍ ቅቡልነትና ምክንያታዊነት ማጉላቱን አስረድተዋል።

በቀጣይም ቀጣናዊ ደህንነት፣ ዓለምአቀፍ ስምምነቶችን፣ በጥናትና ምርምር ላይ የተመሰረተ የዲፕሎማሲ ድርድር አቅምን በማጎልበት ለጥያቄው ምላሽ ማስገኘት እንደሚገባ መክረዋል።

ዜጎችም የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት በተለያዩ አማራጮች ለዓለምአቀፍ ማህበረሰብ በማስገንዘብ ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ቀጣናዊ ሰላምና ደህንነትን በማረጋገጥ የጋራ ዕድገትና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር እንደሚፈጥር ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ መከላከያ ኮሌጅ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አየለ በከሪ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔና ሃያልነት ከነበራት የባህር በር ባለቤትነት ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ታሪካዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ተፈጥሯዊ የባሕር በር ባለቤትነትም ከቀይ ባሕር፣ ገልፍ ኦፍ ኤደን እና ሕንድ ውቅያኖስ ጋር ጭምር የተሰናሰለ እንደነበር አስታውሰዋል።

ከሶስት አስርት ዓመታት በፊት ተዳፍኖ የነበረው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ መነሳቱም ኢትዮጵያን ከስልጣኔና ሃያልነቷ የማስታረቅ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026