የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቀጣናዊ ደህንነትን በማረጋገጥ በትብብር ላይ የተመሰረተ የጋራ ዕድገትን ይፈጥራል

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቀጣናዊ ሰላምና ደህንነትን በማረጋገጥ በትብብር ላይ የተመሰረተ የጋራ ዕድገትን እንደሚፈጥር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና ምሁር ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት ከዓለም ጋር የምትገናኝባቸው የብዝሃ ባሕር በርና የባሕር ዳርቻ መዳረሻ ወደብ ባለቤት እንደነበረች በታሪክ ተሰንዶ ይገኛል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ላይ የተፈጸመው በደል የሚያስቆጭ ነው።

በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ማግስት የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ መነሳቱም ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የህዝብ ቁጥርና የደኅነነት ስጋቶችን መቀልበስ የሚስችል ትብብር ከማጎልበት የሚመነጭ መሆኑን ገልጸዋል።

ሀገራዊ ለውጡም ለበርካታ ዓመታት በህዝብ ልብ ተዳፍኖ የቆየውን ታሪካዊ፣ ፍትሐዊ፣ ሕጋዊና መልክዓ ምድራዊ የባህር በር ባለቤትነት ግልጸኝነት መፍጠሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሰላማዊ፣ ሕጋዊና የጋራ ተጠቃሚነት መርህን ተከትሎ መቅረቡም ዓለምአቀፍ ቅቡልነትና ምክንያታዊነት ማጉላቱን አስረድተዋል።

በቀጣይም ቀጣናዊ ደህንነት፣ ዓለምአቀፍ ስምምነቶችን፣ በጥናትና ምርምር ላይ የተመሰረተ የዲፕሎማሲ ድርድር አቅምን በማጎልበት ለጥያቄው ምላሽ ማስገኘት እንደሚገባ መክረዋል።

ዜጎችም የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት በተለያዩ አማራጮች ለዓለምአቀፍ ማህበረሰብ በማስገንዘብ ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ቀጣናዊ ሰላምና ደህንነትን በማረጋገጥ የጋራ ዕድገትና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር እንደሚፈጥር ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ መከላከያ ኮሌጅ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አየለ በከሪ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔና ሃያልነት ከነበራት የባህር በር ባለቤትነት ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ታሪካዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ተፈጥሯዊ የባሕር በር ባለቤትነትም ከቀይ ባሕር፣ ገልፍ ኦፍ ኤደን እና ሕንድ ውቅያኖስ ጋር ጭምር የተሰናሰለ እንደነበር አስታውሰዋል።

ከሶስት አስርት ዓመታት በፊት ተዳፍኖ የነበረው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ መነሳቱም ኢትዮጵያን ከስልጣኔና ሃያልነቷ የማስታረቅ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026