🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ለመኸር እርሻው እስካሁን ከ4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ እንዳሻው ጀማነህ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በመኸር እርሻ 11 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬትን በማልማት ከ380 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል።
አጠቃላይ በመኸር እርሻ ከሚለማው መሬት ውስጥም 8 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታሩ በኩታ ገጠም የእርሻ ስነ-ዘዴ የሚለማ መሆኑን ጠቁመዋል።
በክልሉ እስካሁን ባለው ሂደት ከ8 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት መታረሱን ጠቅሰው፣ ከዚህ ውስጥ ከ2 ሚሊዮን 823 ሺህ በላይ ሄክታሩ በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን ተናግረዋል።
በምርት ዘመኑ የታቀደውን ግብ ለማሳካት የግብዓት አቅርቦቱ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለመኸር እርሻው ከ14 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቅሰው፣ እስካሁን ከ8 ሚሊዮን 454 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ በሕብረት ሥራ ማህበራትና በዩኒየኖች በኩል እየተሰራጨ መሆኑን ተናግረዋል።
ለማህበራቱና ለዩኒየኖቹ ከደረሰው ማዳበሪያም ከ4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ገልጸዋል።
ከታቀደው 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ውስጥ 378 ሺህ 426 ኩንታሉ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የደረሰ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 355 ሺህ 73 ኩንታሉ ለአርሶ አደሩ በወቅቱ ተከፋፍሏል ብለዋል።
በክልሉ በአሁኑ ወቅት ያለው የዝናብ ሁኔታ መልካም በመሆኑ፣ አርሶ አደሩ ይህንን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በእርሻ ሥራው ላይ በንቃት እየተሳተፈ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
ለመኸር እርሻው ስኬታማነት ከክልል እስከ ታችኛው መዋቅር የሚገኙ አመራሮችና የግብርና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሩ የቅርብ ክትትልና ጠንካራ ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑንም አቶ እንዳሻው ጨምረው ገልጸዋል።
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026