🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) 22ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) እና የአባል ሀገራቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሚኒስትሮች ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ የወቅቱ የትስስሩ ሊቀመንበር (ሰብሳቢ) ስትሆን፤ ዛሬና ነገ በአዲስ አበባ በሚካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ በልዩ ልዩ አጀንዳዎችና ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ትስስሩ 13 ሀገራትን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን፤ በአባል ሀገራቱ መካከል የኤሌክትሪክ ኃይልን በጋራ ለመጠቀም፣ የኃይል ግብይት ለማካሄድ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ታልሞ የተመሠረተ ነው።
ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛንያ፣ ኡጋንዳ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊያና ሊቢያ የጥምረቱ አባል ሀገራት ናቸው።
የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር እ.አ.አ በየካቲት ወር 2005 የተመሠረተ ሲሆን፤ ዋና መሥሪያ ቤቱም በአዲስ አበባ ይገኛል።
ደሴ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መ...
Jul 11, 2026
ደሴ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ወሎ ዞን በግብርናው ዘርፍ ቴክኖሎጂንና አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የተገኘው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ እ...
Jul 10, 2026
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026