የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የጉምሩክ ኮሚሽን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ738 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ

Jul 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 738 ነጥብ 14 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) ገለፁ።

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) የተጠናቀቀውን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ክንውን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።


የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ በበጀት ዓመቱ 725 ነጥብ 27 ቢሊዮን ብር ለማግኘት አቅዶ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል ብለዋል።

በዚህም በተከናወኑ ውጤታማ ሥራዎች 738 ነጥብ 14 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታውቀዋል።

የተገኘው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ77 ነጥብ 56 በመቶ ብልጫ ያስመዘገበ እንደሆነ አመላክተዋል።

ኮሚሽኑ ሀገሪቱ ከቀረጥና ታክስ ተገቢውን ገቢ እንድታገኝ በማድረግ፣ የኮንትሮባንድና ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከልና በመቆጣጠር እንዲሁም የወጪ ንግድ እንዲሳለጥ የሚጠበቅበትን ሚና መወጣቱንም ጠቁመዋል።

የተሰበሰበው ገቢ ከወጪ ንግድ ቀረጥና ታክስ፣ በወጪ ንግድ ላይ ከሚስተዋል የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ እንዲሁም ከሌሎች ኮሚሽኑ ካከናወናቸው ተግባራት የተገኘ መሆኑን አብራርተዋል።

የመንግሥት የፖሊሲ አቅጣጫዎች ለዘርፉ የተመቹ መሆን፣ የተደረጉ ተቋማዊ የሪፎርም ሥራዎች እና አሠራርን በቴክኖሎጂ የማዘመን ተግባራት ለገቢው ማደግ አቅም መፍጠራቸውን ገልጸዋል።

የጉምሩክ ኮሚሽን በ2019 የበጀት ዓመት ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱንም አስታውቀዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሕገወጥ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን የመቆጣጠር ሥራን በማጠናከር፥ ከዘርፉ ጥቅም ማስገኘት ያስቻሉ ውጤታማ ሥራዎች መሰራታቸውን አስገንዝበዋል።

በገቢና በወጪ እቃዎች ላይ በተሰራው የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን የመከላከል ሥራም 28 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር የሚገመቱ ምርቶች መያዛቸውንም አብራርተዋል።

በኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ላይ በተደረገ ቁጥጥር ከተያዙ ምርቶች መካከል ኤሌክትሮኒክስ፣ መድሃኒት፣ አደንዛዥ እጽ፣ የቁም እንስሳት እና ሌሎች እንደሚገኙበት አመላክተዋል።

አሁንም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እያሳደረ ያለውን የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተሰራጭቷል

ደሴ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መ...

Jul 11, 2026

በደቡብ ወሎ ዞን በግብርናው ዘርፍ የተገኘው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ ይቀጥላል

ደሴ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ወሎ ዞን በግብርናው ዘርፍ ቴክኖሎጂንና አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የተገኘው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ እ...

Jul 10, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026