የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ቀልጣፋ የመንግስት አሰራር እንዲሰፍን እያደረገ ነው 

Jul 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ) :-መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ቀልጣፋ የመንግስት አሰራር እንዲሰፍን እያደረገ ነው ሲሉ ምሁራን ገለጹ።

በፌዴራል ደረጃ በአዲስ አበባ የተጀመረው የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በማስፋት ዘመናዊ አገልግሎት እየተፈጠረ ነው።

በዚህም አገልግሎቱ በተጀመረ አንድ ዓመት ባልበለጠ ጊዜ 102 ማዕከላት፣ ሦስት ተንቀሳቃሽና አንድ የተቀናጀ መተግበሪያ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡

በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ አማራጮችም 953 ተቋማትን በማስገባት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ዜጎች አገልግሎት አግኝተዋል፡፡

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥትን አገልግሎት ጥራት በማሻሻል የተገልጋዮችን እርካታ በማሳደግ የመልካም አስተዳደር ሥርዓትን እያሰፈነም ይገኛል፡፡

ኢዜአ ያነጋገራቸው የዘርፉ ምሁራን ፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት በሀገር ደረጃ ትልቅ የለውጥ እርምጃ እንዲሁም የመልካም አስተዳደርና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና አመራር ትምህርት ክፍል መምህር ኡጁሉ ኡኮክ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ህዝቡ ለአንድ አገልግሎት ወደተለያዩ መሥሪያ ቤቶች መመላለስ ሳይጠበቅበት ጊዜውንና ገንዘቡን በአግባቡ እንዲጠቀም የሚያስችል ትልቅ ማሻሻያ ነው።

አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ከብልሹ አሠራር የጸዳ ሥርዓት በመፍጠር ግልጽነትና ተጠያቂነትን እንደሚያሰፍን ገልጸዋል።

ይህ አሰራር ብልሹ አሰራርን በማስቀረት፣ ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥንና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

በተመሳሳይ በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የልማታዊ ተግባቦትና የሚዲያ ጥናት መምህርና ተመራማሪ ዘለቀ ተሾመ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቱ ህብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ላነሳቸው የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠ መሆኑን አንስተዋል።

መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከዚህ ቀደም የነበረን መጉላላት በማስቀረት የተቀላጠፈ፣ ምቹና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለማግኘት ማስቻሉ ለዜጎች ትልቅ እፎይታን የፈጠረ ነው ብለዋል፡፡

አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ማደራጀት የተገልጋዩን ጊዜና ወጪ በመቀነስ የመንግስትን የአሰራር ቅልጥፍናና ከህዝብ ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክር ትልቅ እርምጃ መሆኑን አስታውቀዋል።

አሰራሩ በአፍሪካ ደረጃም በጥሩ አርዓያነት የሚጠቀስ መሆኑን አክለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026

በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል

ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...

Jul 22, 2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ199 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የጠጠር መንገዶች ተገንብተዋል

ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...

Jul 18, 2026