የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢንዱስትሪ ምርቶች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትና ለውጭ ገበያ የማቅረብ አቅም እያደገ መጥቷል-ሚኒስትር መላኩ አለበል

Jul 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ምርቶች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የማሳደግና እና ለውጭ ገበያ የማቅረብ አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።

ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ መድረክ አካሂዷል።


በተጨማሪም ሚኒስቴሩ በበጀት ዓመቱ ወደ ውጭ የመላክ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል።

ሚኒስትር መላኩ አለበል በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ላይ የላቀ ሚና አበርክቷል።

በአምራች ዘርፉ የሚመሩ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን በመቅረጽ ዘርፉን የማነቃቃትና የመደገፍ ሥራ መሠራቱንም ጠቁመዋል።

የኢንዱስትሪ ካውንስል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ተቋቁሞ፣ የኢንዱስትሪዎችን ችግር ከመለየት ጀምሮ በዘላቂነት ተወዳዳሪ ሊሆኑ የሚችሉበትን አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።

በዚህም በዘርፉ የነበሩ ማነቆዎች ለይቶ መፍትሔ በመስጠት ምርት እና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪ ችግሮች እንዲፈታ ታስቦ ተግባራዊ መሆን ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ በዘርፉ ከፍተኛ ውጤቶች መመዝገባቸውን አመላክተዋል።


ይህ ንቅናቄ ሥራ አቁመው የነበሩ በርካታ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲመለሱ ማድረጉን እና አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችም እንዲሰማሩ ማስቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም ገቢ ምርቶችን በመተካት እና የወጭ ንግድን በማሳደግ ረገድ የማይተካ ሚና ማበርከቱን ጠቁመዋል።

የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የፋይናንስ ማነቆ ለመፍታት በተወሰደ እርምጃ፣ ቀደም ሲል 40 ቢሊዮን ብር የነበረውን የብድር መጠን ወደ 115 ቢሊዮን ብር ከፍ ማድረግ ተችሏል።

"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ በተጀመረበት ወቅት ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ይቀርብ የነበረው የውጭ ምንዛሬ መጠን አሁን ላይ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም የኢንዱስትሪዎቻችን ተወዳዳሪነት፣ ምርታማነት፣ ትርፋማነት እና የመስፋፋት ዕድል ከፍ እያለ መምጣቱን ገልጸዋል።

ከ2014 በፊት ኢንዱስትሪዎች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ከ348 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያድኑ አልነበሩም ያሉት ሚኒስትሩ፣ አሁን ላይ ግን 5 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን ተናግረዋል።


ይህም የንግድ ሚዛንን በማጣጣሙ በኩል የኢትዮጵያን ዘላቂ ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱን አብራርተዋል።

በወጭ ንግድ በኩል ቀደም ሲል ይገኝ የነበረው 385 ሚሊዮን ዶላር በዚህ ዓመት ወደ 607 ሚሊዮን ዶላር ማደጉን ጠቁመው፤ የአምራች ዘርፉ ለሥራ ዕድል ፈጠራም ትልቅ አማራጭ እየሆነ መምጣቱን ጠቁመዋል።

በ2019 በጀት ዓመት ከወጭ ንግድ የሚገኘውን ገቢ ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፣ ይህንን ዕቅድ ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሠራም አረጋግጠዋል።

በእውቅናና ምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት አምራቾች በበኩላቸው፤ በኢንዱስትሪው ዘርፍ የተደረጉ የፖሊሲ ማሻሻያዎችና አዳዲስ አቅጣጫዎች ለዘርፉ አዎንታዊ ሚና ማበርከታቸውን ገልጸዋል፡፡


ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል አቶ ሀብታሙ ዳርጌ፤ የተደረጉት የፖሊሲ ማሻሻያዎች የሪፎርም ስራዎች ለአምራቾች ትልቅ ዕድል ይዞ መምጣቱን ጠቅሰዋል፡፡


ማሻሻያዎቹ የምርት መጠናቸውንና ምርታማነታቸውን በከፍተኛ ደረጃ እንዳሳደገላቸው የገለጹት ደግሞ ህይወት ዳመኑ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026

በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል

ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...

Jul 22, 2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ199 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የጠጠር መንገዶች ተገንብተዋል

ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...

Jul 18, 2026