የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል

Aug 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተከናወነው የፍራፍሬ ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበበት መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአካባቢ ጥበቃን ከማረጋገጥ ባሻገር የፍራፍሬ ልማትን በማስፋፋት የዜጎችን የምግብ ዋስትና እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል።

መርሃ ግብሩ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት የሀገሪቱን የደን ሽፋን በተጨባጭ እያሳደገ መሆኑ እሙን ነው።


የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ የተራቆቱ መሬቶችን በማልማትና ለቀጣዩ ትውልድ ምቹ አካባቢን በመፍጠር ረገድ ውጤታማነቱን እያስመሰከረ ይገኛል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር እንደገለጹት፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በፍራፍሬ ልማት የምግብ ዋስትናውን ያረጋገጠና ተጠቃሚነቱን ያሳደገ ቤተሰብ መፍጠር ተችሏል።


የአረንጓዴ አሻራ ትግበራው ለምግብነት የሚውሉ ዛፎችን በመትከል ረገድ ተቋማትን ጨምሮ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።

መርሃ ግብሩ ክልሉ በፍራፍሬ ልማት ያለውን አቅም በአግባቡ እንዲጠቀም ያደረገ ሲሆን የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ ረገድም ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበበት እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በሀድያ ዞን የምስራቅ ባደዋቾ ወረዳ ዌራቡሼራ ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር ኤልያስ መጋቦ በበኩላቸው፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 1 ነጥብ 5 ሄክታር የተራቆተ ማሳቸውን አልምተው ለመጠቀም መቻላቸውን ገልጸዋል።


ማሳቸውን በአቮካዶ፣ በሙዝ፣ በሌሎች የፍራፍሬና የቅመማ ቅመም ሰብሎች በማልማትም ውጤታማ መሆን መቻላቸውን ተናግረዋል።

በዚህም ምርትና ምርታማነታቸው እያደገ በመምጣቱ ያመረቱትን ከቤተሰብ ፍጆታ አልፎ ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዳሳደጉ ገልጸዋል።

የሆሳዕና ከተማ የሄጦ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ትግስት አጋፋሪ፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተሳትፎ በማድረግ በውስን መሬት ላይ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን ማልማታቸውን ነው የሚናገሩት።


ከዚህ ውስጥም የተከሉት የአቮካዶ ችግኝ ደርሶ ፍሬ መስጠት በመጀመሩ ያገኙትን ምርት ከቤት ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026

በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል

ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...

Jul 22, 2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ199 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የጠጠር መንገዶች ተገንብተዋል

ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...

Jul 18, 2026