የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽንና የሪፖርታጅ ግሩፕ የልማት ትብብር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማዘመን ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል

Aug 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽንና የሪፖርታጅ ግሩፕ የልማት ትብብር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማዘመን ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ሉዊጂ ገለጹ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ከዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ሪፖርታጅ ግሩፕ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ሁለገብ የመኖሪያና የንግድ ሕንፃ ለመገንባት የልማት አጋርነት ፕሮጀክት ይፋ አደረጉ።

የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ሉዊጂ በዚህ ወቅት፣ አጋርነቱ የተቋማቱን ስትራቴጂያዊ የልማት አጋርነት በማጠናከር የኢትዮጵያና ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ትብብርን የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም የሀገራቱን ጠንካራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችል ጭምር እንደሆነም ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ ዘመናዊ ከተማን በመገንባት የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል።

የፋውንዴሽኑና የሪፖርታጅ ግሩፕ ትብብርም ዓለም አቀፍ አልሚዎች ኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት መዳረሻ የስበት ማዕከል እያደረጓት እንደሚገኝ ማሳያ ነው ብለዋል።

የሪፖርታጅ ግሩፕ ሊቀመንበር አሪፍ ኢስማኤል በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በሀገራቱ መካከል ያለውን ሁለንተናዊ የልማት ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልጸዋል።

የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሜጀር ጄኔራል ደረጀ መገርሳ፣ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ ፈጣን የከተሜነት ዕድገት ጋር የሚመጣጠን ዘመናዊ ግንባታ እንደሚሆን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ ለሠራዊቱ የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለማሟላት ተጨማሪ የገቢ አቅም የሚገነባ መሆኑን አመልክተዋል።

የሪፖርታጅ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሐናን አሕመድ ኑር እንዳሉት፤ በአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ፊት ለፊት በ23 ሺህ ካሬ ሜትር የሚገነባውን ፕሮጀክት በሦስት ዓመታት ጊዜ ለማጠናቀቅ ይሰራል ብለዋል።

ሕንፃው 1 ሺህ 86 ስቱዲዮ፣ ባለአንድና ባለሁለት መኝታ የመኖሪያ አፓርታማ፣ የንግድ ሱቆች፣ ጂምናዚየም፣ መዋኛ ገንዳ፣ የስፖርት ማዘውተሪያና ሌሎች ዘመናዊ አገልግሎቶችን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱም በመኖሪያና በንግድ ልማት ብቻ ሳይወሰን ለኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ዘመናዊነት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራና ለኢንቨስትመንት መስፋፋት አዲስ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026

በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል

ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...

Jul 22, 2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ199 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የጠጠር መንገዶች ተገንብተዋል

ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...

Jul 18, 2026