
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/2017(ኢዜአ)፦ የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሀገር በቀል ሀብቶችና እውቀቶች ጥበቃ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች የኢንስቲትዩቱን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።

በቲማቲምና በስንዴ ምርት ላይ የሚከሰቱ በሽታዎችን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም ማሽን አስተምሮት በመጠቀም አስቀድሞ የሚለይ እና ለአርሶ አደሮች ምክርን መስጠት ላይ ትኩረት ያደረገ የምርምር ውጤትን ጨምሮ በርካታ የምርምር ስራዎች ምልከታ ተደርጎባቸዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያን ሁኔታ ያገናዘቡ ምርምሮችና የኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ውጤቶች ላይ የጀመረው እንቅስቃሴ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።
በምርምር ስራው የሀገር በቀል ሀብቶች ላይ የሚከሰቱ አደጋዎችን መከላከል፣ እየጠፉ የሚገኙ የሀገር በቀል እውቀቶችን መመለስ እንዲሁም የተሻለ ምርት የሚያስገኙ ዝርያዎች ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባው አመልክተዋል።

ኢንስቲትዩቱ ተልዕኮውን ውጤታማ ለማድረግ ከክልሎች፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ትብብር እንዲያጠናክርም አሳስበዋል።
የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ ተቋሙ የሚሰራቸውን የምርምር ስራዎች በስፋት ለማቅረብ ከግሉ ዘርፍ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር እየሰራ ነው ብለዋል።
በባዮ ቴክኖሎጂ ዘርፍ በአፍሪካ ደረጃ የተሻለ ስራ ለማከናወን እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
ሁሉም የምርምር ተቋማት የሚጠቀሙበት የባዮ ቴክኖሎጂ እና ማቴሪያል ሳይንስ ኮር ላቦራቶሪ እንዲኖር ማድረግ እንደሚገባ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025