
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/2017(ኢዜአ)፦ የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሀገር በቀል ሀብቶችና እውቀቶች ጥበቃ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች የኢንስቲትዩቱን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።

በቲማቲምና በስንዴ ምርት ላይ የሚከሰቱ በሽታዎችን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም ማሽን አስተምሮት በመጠቀም አስቀድሞ የሚለይ እና ለአርሶ አደሮች ምክርን መስጠት ላይ ትኩረት ያደረገ የምርምር ውጤትን ጨምሮ በርካታ የምርምር ስራዎች ምልከታ ተደርጎባቸዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያን ሁኔታ ያገናዘቡ ምርምሮችና የኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ውጤቶች ላይ የጀመረው እንቅስቃሴ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።
በምርምር ስራው የሀገር በቀል ሀብቶች ላይ የሚከሰቱ አደጋዎችን መከላከል፣ እየጠፉ የሚገኙ የሀገር በቀል እውቀቶችን መመለስ እንዲሁም የተሻለ ምርት የሚያስገኙ ዝርያዎች ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባው አመልክተዋል።

ኢንስቲትዩቱ ተልዕኮውን ውጤታማ ለማድረግ ከክልሎች፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ትብብር እንዲያጠናክርም አሳስበዋል።
የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ ተቋሙ የሚሰራቸውን የምርምር ስራዎች በስፋት ለማቅረብ ከግሉ ዘርፍ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር እየሰራ ነው ብለዋል።
በባዮ ቴክኖሎጂ ዘርፍ በአፍሪካ ደረጃ የተሻለ ስራ ለማከናወን እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
ሁሉም የምርምር ተቋማት የሚጠቀሙበት የባዮ ቴክኖሎጂ እና ማቴሪያል ሳይንስ ኮር ላቦራቶሪ እንዲኖር ማድረግ እንደሚገባ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026