
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው።
በጉብኝቱ ላይ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር)፣ በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንዲሁም ሌሎች የክልልና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል።
ከፍተኛ አመራሮቹ በቦንጋ ከተማ በማህበራትና በግለሰቦች የሚከናወኑ የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ሰራዎችን ነው እየጎበኙ የሚገኙት።
አመራሮቹ በጉብኝታቸው በእንሰሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማራ ድርጅትን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።
የድርጅቱ ባለቤት አቶ ዮናስ ገዛሃኝ፤ ስራ ከጀመሩ አስራ አንድ አመታትን ማስቆጠራቸውን ገልጸው በዚህ ወቅትም የተሻለ ደረጃ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ድርጅቱ የወተት ምርቱን ለማሻሻል የመኖ ልማትና ማቀነባበር እንዲሁም ዝርያ ማሻሻል ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በቀን እስከ 550 ሊትር ወተት እንደሚያመርትና ምርቱን በስፋት ለገበያ እያቀረበ መሆኑን አመልክተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026