
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው።
በጉብኝቱ ላይ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር)፣ በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንዲሁም ሌሎች የክልልና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል።
ከፍተኛ አመራሮቹ በቦንጋ ከተማ በማህበራትና በግለሰቦች የሚከናወኑ የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ሰራዎችን ነው እየጎበኙ የሚገኙት።
አመራሮቹ በጉብኝታቸው በእንሰሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማራ ድርጅትን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።
የድርጅቱ ባለቤት አቶ ዮናስ ገዛሃኝ፤ ስራ ከጀመሩ አስራ አንድ አመታትን ማስቆጠራቸውን ገልጸው በዚህ ወቅትም የተሻለ ደረጃ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ድርጅቱ የወተት ምርቱን ለማሻሻል የመኖ ልማትና ማቀነባበር እንዲሁም ዝርያ ማሻሻል ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በቀን እስከ 550 ሊትር ወተት እንደሚያመርትና ምርቱን በስፋት ለገበያ እያቀረበ መሆኑን አመልክተዋል።
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...
Jul 13, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...
Jul 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 7, 2026