
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ እንደሚውል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የዲጂታል ግብይት ስርዓቱን አስተማማኝ ለማድረግ እየተከናወነ ያለው የሳይበር ደሕንነት ስራ ውጤታማ መሆኑም ተገልጿል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን አለማየሁ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት በቀጣይ አመት ሁለተኛው ዙር የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መርሐ ግብር ይጀመራል።
መርሐ ግብሩ ትኩረት ከሚሰጣቸው ተግባራት መካከል በወረቀት ገንዘብ የሚካሔድ ግብይትን ማስቀረትና በወረቀት የሚካሔዱ አገልግሎቶችን የሚያስቀሩ እንደሆነም ነው የገለጹት።
በኢትዮጵያ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስርዓት በስፋት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ምቹ የግብይት ስርዓት ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከዚህ ውስጥም በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የግብይት ስርዓቱን በማዘመን በወረቀት ገንዘብ የሚካሔድ ግብይትን ማስቀረትና ከወረቀት ንክኪ የፀዳ አገልግሎት ተግባራዊ ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለፃ በመጀመሪያው ዙር የዲጂታል ኢትዮጵያ መርሐ ግብር የመንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ነው የገለጹት።
በአሁኑ ወቅትም በ25 የመንግስት ተቋማት 800 በላይ አገልግሎቶች ዲጂታል ቴክኖሎጂን ተጠቅመው እየሰሩ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ባለፉት ጥቂት አመታት ቴሌብርና የንግድ ባንክ የዲጂታል አመራጮችን ጨምሮ በሌሎች የዲጂታል ዘርፎች በተካሔደው ግብይት በትሪሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ማዘዋወር ተችሏል ነው ያሉት።
በመሆኑም የግብይት ስርዓቱን አስተማማኝ ለማድረግ እየተከናወነ ያለው የሳይበር ደህንነት ስራ ውጤታማ በመሆኑ እቅዱን ለማሳካት ምቹ መደላድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል።
እስካሁን ባለው ሒደት ከ11 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ የወሰዱ መሆናቸውንም ነው ሚኒስትር ዴኤታው የተናገሩት።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026