
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
"ህገወጥነትን መከላከልና የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት" በሚል መሪ ሃሳብ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሰባት ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ደብረብርሀን ከተማ እየተካሄደ ነው።
የቢሮው ሃላፊ ኢብራሂም መሐመድ(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የክልሉ መንግስት በስምንት ዋና ዋና ከተሞች አንደኛ ደረጃ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እያካሄደ ይገኛል።
እንዲሁም 15 ሁለተኛ ደረጃ የገበያ ማዕከላት በሌሎች የክልሉ ከተሞች ግንባታቸው መጀመሩን ተናግረዋል።

የገበያ ማዕከላቱ መገንባት ህገ ወጥ ንግድና ደላlaን በመከላከል የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርትን ከአምራቹ በቀጥታ በመረከብ ለሸማቹ እንዲደርስና ገበያን ለማረጋጋት እንደሚያግዙ ተናግረዋል።
ማዕከላቱ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ በየደረጃው የሚገኙ አመራር አባላትና የዘርፉ ባለሙያዎች ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት፤ ገበያን ለማረጋጋት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ ወይዘሮ ይርጋለም ምስጋናው በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ 49 ሚሊየን ብር በመመደብ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማቅረብ ተችሏል።
የኑሮ ውድነትን ለመቀነስም አምራችና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኝ የመጀመሪያ ደረጃ የገበያ ማዕከል ግንባታ በ196 ሚሊየን ብር ወጪ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በመድረኩ ላይ ከክልል፣ ከዞንና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ንግድና ገበያ ልማት ዘርፍ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ነው።
ተሳታፊዎቹ ቀደም ሲል በደብረብርሃን ከተማ ገበያን ለማረጋጋት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ተመልክተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026