የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢቢሲ አሁን ካለው ደረጃ ወደ ተሻለ ምእራፍ እንዲሸጋገር መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/20017(ኢዜአ)፦ ኢቢሲ አሁን ካለው ደረጃ ወደ ተሻለ ምእራፍ እንዲሸጋገር መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ሸጎሌ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና መሥሪያ ቤት ጎብኝተናል ብለዋል፡፡

ኢቢሲ የኢትዮጵያን ታሪክ፣ ባህልና ማህበራዊ እሴቶች በማስተዋወቅ እና ለመልካም ገፅታ ግንባታ እያደረገ ያለው ጥረት ለሌሎች መገናኛ ብዙኃን ምሳሌ መሆን የሚችል ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡


ተቋሙ ዘመኑን የዋጀ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ከመገንባት ባሻገር "ወደ ይዘት" በሚል መሪ ቃል በጀመረው የይዘትና የአቀራረብ ማሻሻያ ተደራሽነቱን ለማስፋት እየሠራቸው የሚገኙ ተግባራት አበረታች ናቸው ነው ያሉት፡፡

ኢቢሲ በተለያዩ ክልሎች አዳዲስ ስቱዲዮዎችን ገንብቶ ወደ ሥራ ማስገባቱ የኢትዮጵያን አዎንታዊ መልክ ለማጉላትና የወል ትርክትን ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል ብለዋል፡፡


ተቋሙ ተአማኒና ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ ለመሆን፣ የሀገርን ታሪክና ባህል ለማስከበር እና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲፈጠር፤ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

ኢቢሲ አሁን ካለው ደረጃ ወደ ተሻለ ምእራፍ እንዲሸጋገር መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ሲሉም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.