
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/20017(ኢዜአ)፦ ኢቢሲ አሁን ካለው ደረጃ ወደ ተሻለ ምእራፍ እንዲሸጋገር መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ሸጎሌ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና መሥሪያ ቤት ጎብኝተናል ብለዋል፡፡
ኢቢሲ የኢትዮጵያን ታሪክ፣ ባህልና ማህበራዊ እሴቶች በማስተዋወቅ እና ለመልካም ገፅታ ግንባታ እያደረገ ያለው ጥረት ለሌሎች መገናኛ ብዙኃን ምሳሌ መሆን የሚችል ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ተቋሙ ዘመኑን የዋጀ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ከመገንባት ባሻገር "ወደ ይዘት" በሚል መሪ ቃል በጀመረው የይዘትና የአቀራረብ ማሻሻያ ተደራሽነቱን ለማስፋት እየሠራቸው የሚገኙ ተግባራት አበረታች ናቸው ነው ያሉት፡፡
ኢቢሲ በተለያዩ ክልሎች አዳዲስ ስቱዲዮዎችን ገንብቶ ወደ ሥራ ማስገባቱ የኢትዮጵያን አዎንታዊ መልክ ለማጉላትና የወል ትርክትን ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል ብለዋል፡፡

ተቋሙ ተአማኒና ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ ለመሆን፣ የሀገርን ታሪክና ባህል ለማስከበር እና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲፈጠር፤ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
ኢቢሲ አሁን ካለው ደረጃ ወደ ተሻለ ምእራፍ እንዲሸጋገር መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026