
ሆሳዕና ፡ ታህሳስ 26/2017(ኢዜአ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችና ምርጥ ዘር ማፍለቅ ላይ ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ።
በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በግብርናው ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችንና ማነቆዎችን በመለየት ችግር ፈቺ የምርምር እቅድ ማዘጋጀት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር ፤ በክልሉ በግብርና ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም ማዘመን ይገባል ብለዋል ።
በግብርናው ዘርፍ ያሉ ዕድሎችን በአግባቡ ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ማስደገፍ ተገቢ መሆኑን አመልክተዋል።
ይህም ዕድሎችን ወደ ውጤት በመቀየር ከቤተሰብ እስከ ማህበረሰብ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል ።
በክልሉ ግብርናን በማዘመን በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት እየተደረገ የሚገኘውን ጥረት በማገዝ ተመራማሪዎች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለባቸወም ገልጸዋል።
የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ተረፈ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በክልሉ የሚከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎች በምርምር የታገዙ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችና ምርጥ ዘር ማፍለቅ እንዲሁም በሂደት የሚገጥሙ የተባይና መሰል በሽታ ቁጥጥር ላይ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።
በክልሉ በዘርፉ ባሉ ማነቆዎች ላይ ጥናት መካሄዱን ጠቅሰው፤ በዚህም ለተለዩ ማነቆዎች የመፍትሄ ሃሳቦችና የቀጣይ እርምጃዎች ላይ በአሁኑ መድረኩ ውይይት እንደሚደረግበት አመልክተዋል።
የክልሉ ፣ የዞንና የልዩ ወረዳ የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አባላት በውይይት መድረኩ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025