የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በትግራይ ክልል በ41 ማዕከላት ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እየተከናወነ ነው

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ታህሳስ 30/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ በክልል በ41 ቋሚና ተንቀሳቃሽ ማዕከላት ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮ-ቴሌኮም የሰሜን ሪጅን አስታወቀ።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025ን ለማሳካት አስቻይ ከሆኑት ምሰሶዎች መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተደራሽ፣ አካታች እና በመረጃ የሚመራ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመፍጠር የሚያስችል ዋነኛ ምሰሶ መሆኑም እንዲሁ።

ፋይዳ በባዮሜትሪክ መረጃዎች ወጥ በሆነ ማንነት መታወቅ፤ መተማመን በመፍጠር አንድ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባትም ጉልህ አንድምታ እንዳለውም ይታመናል፡፡

ኢትዮ-ቴሌኮም ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ማስጀመሩ ይታወቃል፡፡

በኢትዮ-ቴሌኮም የሰሜን ሪጅን ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ሙሉ ወልደስላሴ፤ ዲስትሪክቱ በትግራይ ክልል ባለፉት ስምንት ወራት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን ጨምሮ የዲጂታል መታወቂያ ሕትመት አገልግሎትን በመስጠት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡

የሰሜን ሪጅን ዲስትሪክት በ26 ቋሚና 15 ተንቀሳቃሽ ማዕከላት አገልግሎቱን በመስጠት ላይ እንደሚገኝም ነው የገለጹት፡፡

ደንበኞች የኩባንያውን አገልግሎት ለማግኘት ወደ ማዕከላት ሲያመሩ ብሎም በተንቀሳቃሽ ማዕከላት ባሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎቱን እንዲያገኙ በመደረግ ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ዲስትሪክቱ እስካሁን ከ235 ሺህ በላይ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው፥ በቀጣይ ማዕከላቱን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሕብረተሰቡ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ያለውን ጠቀሜታ እንዲረዳ የግንዛቤ ማስጨበጭ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ነው የጠቆሙት ፡፡

በሪጅኑ በሚገኙ ማዕከላት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሲመዘገቡ ከነበሩት መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው ወይዘሮ ራህዋ ገብረስላሴ እና ተስፈየ ገብረመስቀል፤ ብሔራዊ መታወቂያን ለባንክ አገልግሎት እንዲሁም ፓስፖርት ለማውጣት እንደሚጠቀሙበት ገልጸዋል፡፡

ሌሎችም ብሔራዊ መታወቂያ ለሁሉም አገልግሎት ጠቃሚ መሆኑን በመረዳት ምዝገባ ማከናወን እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

ሌላኛዋ ተመዝጋቢ ዮርዳኖስ ረዳ እና ወይዘሮ ለምለም ኪዳነማርያም፤ ፋይዳ መታወቂያ ህጋዊነትን ለማረጋገጥ ጠቀሜታ እንዳለው ጠቁመው፥ በመንግስትም ሆነ በግል ተቋማት አገልግሎት ለማግኘት እንደሚረዳ ገልጸዋል፡፡

የብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ከዚህም ባለፈ ዘርፍ ብዙ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ በእያንዳንዳችን እጅ መድረስ ያለበት ወሳኝ ጉዳይ መሆኑንም ተገልጋዮቹ አንስተዋል።

የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የማጭበርበርና ህገ ወጥ አሰራሮችን በመከላከል ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል መሆኑም ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026