
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በሀረሪ ክልል የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ስራ ለማስጀመር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
አቶ ኦርዲን በድሪ በሀረር ከተማ በ1 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታው እየተካሄደ የሚገኘውን የአባድር ፕላዛ ፕሮጀክት ጎብኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በመስክ ምልከታው ላይ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ ጥሩ በሚባል የግንባታ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን አመላክቷል።

በክልሉ የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ በጥራት እና ፍጥነት ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ አጠናቆ ስራ ለማስጀመር እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
በተለይ በቅርቡ ተቋቁሞ ወደ ስራ የገባው የሀረሪ ኮንስትራክሽን እና መሰረተ ልማት ግንባታ ድርጅት የፕሮጀክት ግንባታ ስራዎችን በምሽት ጭምር በማከናወን የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ ማስቻሉን ገልፀዋል።
ድርጅቱ በግል የኮንስትራክሽን ድርጅቶች በስራ መደራረብ ምክንያት በፕሮጀክቶች ላይ ይስተዋል የነበረውን መዘግየት በማስቀረት ጥሩ ተሞክሮ እና ልምድ የተወሰደበት መሆኑንም ጠቁመዋል።

አክለውም ለፕሮጀክቱ ስኬታማነት ግዜን በአግባቡ በመጠቀም አመራሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ከግንባታ ስራው ጎን ማከናወን እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ ግንባታቸው ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ ህንፃዎችን በፍጥነት ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል።
በ1 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ የሚገኘው የአባድር ፕላዛ ግሪነሪ፤ አንፊ ቲያትር፤ ፋውንቴኖች እና ሌሎች መናፈሻዎችን የያዘ መሆኑ ተመላክቷል።
በመስክ ምልከታው የክልሉ ካቢኔ አባላት መገኘታቸውንም ተጠቁሟል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025