
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በሀረሪ ክልል የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ስራ ለማስጀመር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
አቶ ኦርዲን በድሪ በሀረር ከተማ በ1 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታው እየተካሄደ የሚገኘውን የአባድር ፕላዛ ፕሮጀክት ጎብኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በመስክ ምልከታው ላይ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ ጥሩ በሚባል የግንባታ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን አመላክቷል።

በክልሉ የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ በጥራት እና ፍጥነት ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ አጠናቆ ስራ ለማስጀመር እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
በተለይ በቅርቡ ተቋቁሞ ወደ ስራ የገባው የሀረሪ ኮንስትራክሽን እና መሰረተ ልማት ግንባታ ድርጅት የፕሮጀክት ግንባታ ስራዎችን በምሽት ጭምር በማከናወን የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ ማስቻሉን ገልፀዋል።
ድርጅቱ በግል የኮንስትራክሽን ድርጅቶች በስራ መደራረብ ምክንያት በፕሮጀክቶች ላይ ይስተዋል የነበረውን መዘግየት በማስቀረት ጥሩ ተሞክሮ እና ልምድ የተወሰደበት መሆኑንም ጠቁመዋል።

አክለውም ለፕሮጀክቱ ስኬታማነት ግዜን በአግባቡ በመጠቀም አመራሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ከግንባታ ስራው ጎን ማከናወን እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ ግንባታቸው ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ ህንፃዎችን በፍጥነት ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል።
በ1 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ የሚገኘው የአባድር ፕላዛ ግሪነሪ፤ አንፊ ቲያትር፤ ፋውንቴኖች እና ሌሎች መናፈሻዎችን የያዘ መሆኑ ተመላክቷል።
በመስክ ምልከታው የክልሉ ካቢኔ አባላት መገኘታቸውንም ተጠቁሟል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026