
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- የካፒታል ገበያ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ገበያ መሪ ተዋናይ እንድትሆን ያስችላታል ሲሉ የናይጄርያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተሚ ፖፖላ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን ትናንት በይፋ አስጀምረዋል፡፡

የናይጄርያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ሥራ አስፈፃሚ ተሚ ፖፖላ በመርሀ ግብሩ ወቅት በሰጡት ማብራሪያ በኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በአፍሪካ ገበያ የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
በናይጄርያ ከ62 አመት በፊት የተጀመረው የካፒታል ገበያ በተወሰነ ዘርፍ ላይ ከማተኮር ወጥቶ አማራጭ ገበያ እያፈላለገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ድርሻ በመሳተፋቸው መደሰታቸውን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ዘርፉ ሁሉንም በንቃት በማሳተፍ ምርትና አገልግሎቶችን በስፋት ማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መንግሥት ምቹ ፖሊሲዎችና አሰራሮችን በመዘርጋት ለመሰረተ ልማት ማስፋፊያ የሚሆን ገቢ መሰበሰብ የግሉ ዘርፍ ደግሞ የተፈጠረለትን እድል በመጠቀም ገበያውን በስፋት መቀላቀል አለበት ብለዋል፡፡
በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለው ትብብር መጎልበት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቋቋም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያስቀጥል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዓለም ላይ ያለ የካፒታል ገበያ ውጤታማ ኢኮኖሚ መገንባት አስቸጋሪ መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ስኬት ላይ ለመድረስ የሌሎች ሀገራትን ልምድ መውሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለሥራ እድል ፈጠራ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ገንቢ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ገበያው ኢትዮጵያን በአፍሪካ ገበያ መሪ ተዋናይ መሆን የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥርላት እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026