
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- የካፒታል ገበያ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ገበያ መሪ ተዋናይ እንድትሆን ያስችላታል ሲሉ የናይጄርያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተሚ ፖፖላ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን ትናንት በይፋ አስጀምረዋል፡፡

የናይጄርያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ሥራ አስፈፃሚ ተሚ ፖፖላ በመርሀ ግብሩ ወቅት በሰጡት ማብራሪያ በኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በአፍሪካ ገበያ የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
በናይጄርያ ከ62 አመት በፊት የተጀመረው የካፒታል ገበያ በተወሰነ ዘርፍ ላይ ከማተኮር ወጥቶ አማራጭ ገበያ እያፈላለገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ድርሻ በመሳተፋቸው መደሰታቸውን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ዘርፉ ሁሉንም በንቃት በማሳተፍ ምርትና አገልግሎቶችን በስፋት ማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መንግሥት ምቹ ፖሊሲዎችና አሰራሮችን በመዘርጋት ለመሰረተ ልማት ማስፋፊያ የሚሆን ገቢ መሰበሰብ የግሉ ዘርፍ ደግሞ የተፈጠረለትን እድል በመጠቀም ገበያውን በስፋት መቀላቀል አለበት ብለዋል፡፡
በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለው ትብብር መጎልበት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቋቋም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያስቀጥል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዓለም ላይ ያለ የካፒታል ገበያ ውጤታማ ኢኮኖሚ መገንባት አስቸጋሪ መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ስኬት ላይ ለመድረስ የሌሎች ሀገራትን ልምድ መውሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለሥራ እድል ፈጠራ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ገንቢ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ገበያው ኢትዮጵያን በአፍሪካ ገበያ መሪ ተዋናይ መሆን የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥርላት እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025