
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2017(ኢዜአ)፦ የጅማ - ጭዳ 80 ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ አስፋልት የማንጠፍ ምዕራፍ መሸጋገሩን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ገልጿል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የኦሮሚያ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች ሶስት ወረዳዎችን የሚያስተሳስር መሆኑም ተመላክቷል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ የ10 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ስራ መከናወኑንም አስተዳደሩ አስታውቋል።
መንገዱ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ እና የሃላል ኬላ መዳረሻ በመሆኑ ለቱሪስቶች ምቹ ከማድረግ አኳያ ጉልህ አስተዋጽዖ የሚያበረክት መሆኑንም ጠቁሟል።

በተጨማሪም የ14 ኪሎ ሜትር ሰብቤዝ፣ 11 ኪሎ ሜትር ቤዝኮርስ እና የ52 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ሥራዎች መሰራታቸውንና የአንድ ድልድይ ግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኝም ገልጿል።
የመንገዱ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸም 31 በመቶ መድረሱንም አስተዳደሩ አስታውቋል።
የፕሮጀክቱን የተሻለ አፈጻጸም አጠናክሮ ለማስቀጠል በማሽነሪ፣ የሰለጠነ ባለሞያ ቅጥር እና በግብአት በኩል በቂ ዝግጅት መደረጉን ቦታው ድረስ በተደረገ ቅኝት መመልከት መቻሉንም አረጋግጧል።
በተጨማሪም ግንባታው የአካባቢውን ሥነ-ምኅዳር ባገናዘበ መልኩ የአካባቢ እና የማኅበራዊ ደኅንነት መርሆዎችን ተከትሎ በጥንቃቄ እየተከናወነ ይገኛል ብሏል አስተዳደሩ።

ቻይና ቲሲጁ ኢንጂነሪንግ ግንባታውን እያከናወነ መሆኑንና ኪዮንግዶንግ ኢንጂነሪንግ፣ ኦሪየንታል ኮንሰልቲንግ እና ኮር ኮንሰልቲንግ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በጥምረት እንደሚሰሩም ጠቁሟል።
ለግንባታው የተመደበው 2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በአፍሪካ የልማት ፈንድ እና በጃፓን ዓለም-አቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚሸፈንመ አስተዳደሩ በመረጃው አስታውቋል።
መንገዱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ከጅማ ከተማ እስከ ጭዳ ከተማ ለመድረስ የሚወስደውን 4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ከአንድ ሰዓት ተኩል ባነሰ መግባት እንደሚያስችልና የጅማ፣ ዴዶ፣ ሚቴሶ እና መሰል ከተሞች ትስስርን በማጠናከር ምርት በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ እንደሚያስችልም በመረጃው ተመላክቷል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026