
አዲስ አበባ፤ጥር 6 /2017(ኢዜአ)፡-የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅን በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ።
6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 15ኛ መደበኛ ጉባዔ እየተካሄደ ነው።
በዚሁ ጊዜ የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ በፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ የቀረበ ሲሆን የምክር ቤቱ አባላት በአዋጁ ላይ ያላቸውን ጥያቄ እና አስተያየት አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጅጌ(ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ በኢትዮጵያ ከሚመነጨው ሀብት አኳያ የሚሰበሰበው ገቢ በቂ አለመሆኑን ገልጸዋል።
በታክስ የሚሰበሰበው ገቢ ለጥቅል አገራዊ ምርት (ጂ ዲ ፒ) ያለው አስተዋጽኦ ከ7 በመቶ እንደማይበልጥ ጠቅሰው ይህም ከሳሃራ በታች ካሉ ሀገራት ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ መሆኑን አብራርተዋል።
ገቢ የመሰብሰብ አቅም ሊያድግ እንደሚገባ የገለጹት ሚኒስትሩ አዋጁ ታክስ የመሰብሰብ አቅምን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።
አዋጁ የታክስ መሰረትን ለማስፋት፣ የመንግሥት መሰረተ ልማት አቅርቦት አቅምን ለማሳደግ እንዲሁም ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመተግበር አጋዥ መሆኑን አመላክተዋል።
አንገብጋቢ ለሆኑ የሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የገቢ አቅምን ማሳደግ ቁልፍ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ ለዚህም የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጁ ሥራ ላይ መዋል የላቀ ፋይዳ አለው ብለዋል።
ምክር ቤቱ በንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጁ ዙሪያ በቀረቡ ጥያቄና አስተያየቶች ላይ ከተወያየ በኋላ አዋጁን መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026