የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>የእንሰት ተክል የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት እንዲሳካ ትልቅ ፋይዳ አለው--የዘርፉ ባለሙያዎች</p>

Jan 15, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ ጥር 6/2017 (ኢዜአ)፡-የእንሰት ተክል የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት እንዲሳካ ከማገዝ አንጻር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አስተያየታቸውን የሰጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ።

የእንሰት ተክል ምርታማነትን በመቀነስ አሉታዊ ጫና እያሳደረ ያለውን የእንሰት አጠውልግ በሽታ ለመከላከል ግብርና ሚኒስቴር የበኩሉን እየተወጣ መሆኑንም አስታውቋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የዘርፉ ባለሙያዎች እንደገለጹት፤ የእንሰት ተክል የምግብ ዋስትናን እንዲሁም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ትልቅ ፋይዳ አለው።


በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ተመራማሪ አምባሳደር ፕሮፈሰር አድማሱ ፀጋዬ እንሰት ከሌሎች የሆርቲካልቸር ሰብሎች ይልቅ ለምግብ ዋስትናና ለዘላቂ ልማት መረጋገጥ የማይተካ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

በሀገራችን በተለያዩ ክልሎች ቁጥሩ 20 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ እንሰትን ለምግብነት እንደሚጠቀም ጠቅሰው፤ ዕሴትን ጨምሮ በማምረት የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት የጎላ ፋይዳ እንዳለውም ተናግረዋል።

እንሰት ውሃን አምቆ ስለሚይዝ ድርቅን የመቋቋምና የመሬት ለምነትን የመጠበቅ አቅሙ የጎላ መሆኑን ተናግረው፣ ከሌሎች ምግቦች ጋር ሲታይ በንጥረ ነገር ይዘቱ የላቀ መሆኑን አስረድተዋል።

ዓመቱን ሙሉ የሚመረት፣ በምርታማነቱ ከፍተኛ የሆነና በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገኝ መሆኑ ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑንም አምባሳደር ፕሮፈሰር አድማሱ ገልጸዋል።

ተረፈ ምርቶቹ ለእንስሳት መኖነት የሚውል በመሆኑ ድርብ ጥቅም እንዳለውም አንስተዋል።

በእንሰት ላይ የተከሰተው በሽታ ለመከላከል ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባም አመልክተዋል።

በግብርና ሚኒስቴር የሆርቲካልቸር ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብደላ ነጋሽ በበኩላቸው፤ የእንሰት ሰብል የህዝቡን የምግብ ዋስትና በማረጋገጡ ረገድ ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል።


የእንሰት አጠውልግ በሽታ በምርትና ምርታማነት ላይ እያሳደረ ያለውን አሉታዊ ጫናና የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ህዝቡን ያሳተፈ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በሽታውን ከመከላከል ባለፈ የእንሰት ዝርያን የማሻሻልና በእንሰት የሚለማን መሬት የማስፋት ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

አርሶ አደሩ ወደማሳ ሲገባ ከአለባበስ ጀምሮ ተገቢ ጥንቃቄ በማድረግ የማሳ ንጽህናን በመጠበቅ በሽታውን መግታት እንዳለበት የገለጹት ደግሞ በሚኒስቴሩ የእፅዋት ጥበቃ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ በላይነህ ንጉሤ ናቸው።


የእንሰት ሰብል በሀገሪቱ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማና በኦሮሚያ ክልሎች በስፋት የሚመረት ሲሆን ለምግብ ዋስትናና ለውጭ ምንዛሬ የጎላ ድርሻ እንዳለው ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026