ሐረማያ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በምርምር ያገኛቸውንና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ ምርጥ የድንችና የሰብል ዝርያዎችን ለተጠቃሚዎች ሊያሰራጭ መሆኑን አስታወቀ።
ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው በተጓዳኝ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
በዩኒቨርሲቲው የኢንተርፕራይዝ ልማት ዳይሬክተር ከተማ በቀለ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የድንችና የሰብል ዝርያዎችን አባዝቷል።
ዩኒቨርሲቲው በዋናው ግቢ በሚገኘው 106 ሄክታር መሬት ላይ ያባዛቸውን የድንች፣ የበቆሎ፣ ማሽላ፣ ቦሎቄ፣ ስንዴና ሌሎች የሰብል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማሰራጨት ተዘጋጅቷል ብለዋል።
የተሻሻሉ ዝርያዎቹን በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ የማላመድ ስራ ማከናወኑንም አክለዋል።
ከምርጥ ዝርያዎቹ መካከል በተለይም 'ቡቡ' እና 'ጉደኔ' የተባሉት የድንች ዝርያዎች በሽታን በመቋቋም በሄክታር እስከ 350 ኩንታል ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
'መልካሳ 3' እና 'BH-560' የተባሉት የበቆሎ ምርጥ ዝርያዎችም በሄክታር ከ55 እስከ 60 ኩንታል መስጠት የሚችሉ እንደሆነ አስረድተዋል።
በተጨማሪም በዋናው ግቢ በሚገኘው 11 ሄክታር የምርምር መሬት ላይ የአተር ምርጥ ዘር የማባዛት ስራ እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
የዘር ብዜት ሲከናወንባቸው የቆዩና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡትን 4ሺህ 600 ኩንታል የድንች እና የሰብል ዝርያዎች በሐረሪ ክልል፣ ምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች በዘር ብዜት ለተሰማሩ ማህበራትና ለአርሶ አደሩ በቅርቡ እንደሚሰራጩም ተናግረዋል።
ዩኒቨርሲቲው ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 5ሺህ 230 ኩንታል የተሻሻሉ ምርጥ የድንችና እና የሰብል ዝርያዎችን በሐረሪ ክልል፣ ምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች በዘር ብዜት ለተሰማሩ ማህበራትና አርሶ አደሮች ማሰራጨቱን አያይዘው ገልጸዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025