
ሐረማያ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በምርምር ያገኛቸውንና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ ምርጥ የድንችና የሰብል ዝርያዎችን ለተጠቃሚዎች ሊያሰራጭ መሆኑን አስታወቀ።
ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው በተጓዳኝ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።

በዩኒቨርሲቲው የኢንተርፕራይዝ ልማት ዳይሬክተር ከተማ በቀለ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የድንችና የሰብል ዝርያዎችን አባዝቷል።
ዩኒቨርሲቲው በዋናው ግቢ በሚገኘው 106 ሄክታር መሬት ላይ ያባዛቸውን የድንች፣ የበቆሎ፣ ማሽላ፣ ቦሎቄ፣ ስንዴና ሌሎች የሰብል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማሰራጨት ተዘጋጅቷል ብለዋል።
የተሻሻሉ ዝርያዎቹን በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ የማላመድ ስራ ማከናወኑንም አክለዋል።

ከምርጥ ዝርያዎቹ መካከል በተለይም 'ቡቡ' እና 'ጉደኔ' የተባሉት የድንች ዝርያዎች በሽታን በመቋቋም በሄክታር እስከ 350 ኩንታል ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
'መልካሳ 3' እና 'BH-560' የተባሉት የበቆሎ ምርጥ ዝርያዎችም በሄክታር ከ55 እስከ 60 ኩንታል መስጠት የሚችሉ እንደሆነ አስረድተዋል።
በተጨማሪም በዋናው ግቢ በሚገኘው 11 ሄክታር የምርምር መሬት ላይ የአተር ምርጥ ዘር የማባዛት ስራ እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የዘር ብዜት ሲከናወንባቸው የቆዩና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡትን 4ሺህ 600 ኩንታል የድንች እና የሰብል ዝርያዎች በሐረሪ ክልል፣ ምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች በዘር ብዜት ለተሰማሩ ማህበራትና ለአርሶ አደሩ በቅርቡ እንደሚሰራጩም ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 5ሺህ 230 ኩንታል የተሻሻሉ ምርጥ የድንችና እና የሰብል ዝርያዎችን በሐረሪ ክልል፣ ምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች በዘር ብዜት ለተሰማሩ ማህበራትና አርሶ አደሮች ማሰራጨቱን አያይዘው ገልጸዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026