አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ በሀዋሳ ከተማ መናኸሪያዎች የተተገበረው ኤሌክትሮኒክ ቲኬት የመናኸሪያ አገልግሎት አሰጣጥን ምቹና ቀልጣፋ እንዲሆን ማስቻሉን የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።
ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሐዋሳ ከተማ መናኸሪያዎች አገልግሎትን ለማዘመን የተተገበሩ ዘመናዊ አሰራሮችን ተመልክተዋል።
የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፤ የትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን የመናኸሪያዎችን ደረጃ የማሻሻልና በቴክኖሎጂ የማስደገፍ ሥራ እየተከናወነ ነው።
የመናኸሪያዎችን የትኬት አገልግሎት ፈጣን፣ ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ የኤሌክትሮኒክ ወይም ኢ-ትኬት ሥርዓት መተግበሩን ጠቅሰዋል።
ይህም ከታሪፍ በላይ ማስከፈል፣ ትርፍ መጫን፣ ከተመደቡበት የስምሪት መሥመር ውጪ መጫንና መሰል የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን መቅረፉን ገልጸዋል።
በቀጣይም ከሐዋሳ ከተማ ተሞክሮን በክልሉ ዞኖች እና ወረዳዎች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025