
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ በሀዋሳ ከተማ መናኸሪያዎች የተተገበረው ኤሌክትሮኒክ ቲኬት የመናኸሪያ አገልግሎት አሰጣጥን ምቹና ቀልጣፋ እንዲሆን ማስቻሉን የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።
ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሐዋሳ ከተማ መናኸሪያዎች አገልግሎትን ለማዘመን የተተገበሩ ዘመናዊ አሰራሮችን ተመልክተዋል።
የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፤ የትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን የመናኸሪያዎችን ደረጃ የማሻሻልና በቴክኖሎጂ የማስደገፍ ሥራ እየተከናወነ ነው።
የመናኸሪያዎችን የትኬት አገልግሎት ፈጣን፣ ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ የኤሌክትሮኒክ ወይም ኢ-ትኬት ሥርዓት መተግበሩን ጠቅሰዋል።
ይህም ከታሪፍ በላይ ማስከፈል፣ ትርፍ መጫን፣ ከተመደቡበት የስምሪት መሥመር ውጪ መጫንና መሰል የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን መቅረፉን ገልጸዋል።
በቀጣይም ከሐዋሳ ከተማ ተሞክሮን በክልሉ ዞኖች እና ወረዳዎች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025