ሐረር፤ ጥር 10/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በሐረሪ ክልል የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማነቃቃቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ።
የኢትዮጵያ ታምርት ክልል አቀፍ ንቅናቄ መድረክ በሐረሪ ክልል እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ ከፍተኛ መነቃቃት ተፈጥሯል።
በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚታዩ ማነቆዎችን በመፍታት ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻሉን ገልጸዋል።
በንቅናቄው ተዘግተው የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መመለሳቸውን ጠቅሰው በክልሉ የሚገኙ አነስተኛ ኢንዳስትሪዎች ወደ መካከለኛ፤ መካከለኛዎቹ ደግሞ ወደ ከፍተኛ ኢንዳስትሪ እንዲሸጋገሩ ዕድል መስጠሩንም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ስኬታማ እንዲሆን የክልሉ መንግስት በዘርፉ ለተሰማሩት አካላት ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው የተጀመረው አበረታች ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል።
የሐረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዳስትሪ ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡስማኢል ዩስፍ በበኩላቸው በክልሉ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በምግብና መጠጥ ማቀነባበር፣ በእንጨትና ብረታ ብረትና በሌሎች የተሰማሩ አምራቾች እየተበራከቱ ነው ብለዋል።
በዚህም በክልሉ 165 አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዳስትሪዎች በተለያዩ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው የማምረት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።
በተለይ አምራች እንዳስትሪው የማምረት አቅማቸውን የማጎልበትና የሚገጥማቸውን ችግር የመቅረፍ ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
"ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ክልላዊ የንቅናቄ መድረክ በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራር አካላትና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025