
ሐረር፤ ጥር 10/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በሐረሪ ክልል የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማነቃቃቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ።
የኢትዮጵያ ታምርት ክልል አቀፍ ንቅናቄ መድረክ በሐረሪ ክልል እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ ከፍተኛ መነቃቃት ተፈጥሯል።
በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚታዩ ማነቆዎችን በመፍታት ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻሉን ገልጸዋል።
በንቅናቄው ተዘግተው የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መመለሳቸውን ጠቅሰው በክልሉ የሚገኙ አነስተኛ ኢንዳስትሪዎች ወደ መካከለኛ፤ መካከለኛዎቹ ደግሞ ወደ ከፍተኛ ኢንዳስትሪ እንዲሸጋገሩ ዕድል መስጠሩንም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ስኬታማ እንዲሆን የክልሉ መንግስት በዘርፉ ለተሰማሩት አካላት ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው የተጀመረው አበረታች ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል።

የሐረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዳስትሪ ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡስማኢል ዩስፍ በበኩላቸው በክልሉ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በምግብና መጠጥ ማቀነባበር፣ በእንጨትና ብረታ ብረትና በሌሎች የተሰማሩ አምራቾች እየተበራከቱ ነው ብለዋል።
በዚህም በክልሉ 165 አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዳስትሪዎች በተለያዩ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው የማምረት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።
በተለይ አምራች እንዳስትሪው የማምረት አቅማቸውን የማጎልበትና የሚገጥማቸውን ችግር የመቅረፍ ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
"ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ክልላዊ የንቅናቄ መድረክ በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራር አካላትና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026