የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ዘርፉን አነቃቅቷል- አቶ ኦርዲን በድሪ</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS


ሐረር፤ ጥር 10/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በሐረሪ ክልል የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማነቃቃቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ።

የኢትዮጵያ ታምርት ክልል አቀፍ ንቅናቄ መድረክ በሐረሪ ክልል እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ ከፍተኛ መነቃቃት ተፈጥሯል።

በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚታዩ ማነቆዎችን በመፍታት ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻሉን ገልጸዋል።

በንቅናቄው ተዘግተው የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መመለሳቸውን ጠቅሰው በክልሉ የሚገኙ አነስተኛ ኢንዳስትሪዎች ወደ መካከለኛ፤ መካከለኛዎቹ ደግሞ ወደ ከፍተኛ ኢንዳስትሪ እንዲሸጋገሩ ዕድል መስጠሩንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ስኬታማ እንዲሆን የክልሉ መንግስት በዘርፉ ለተሰማሩት አካላት ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው የተጀመረው አበረታች ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል።


የሐረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዳስትሪ ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡስማኢል ዩስፍ በበኩላቸው በክልሉ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በምግብና መጠጥ ማቀነባበር፣ በእንጨትና ብረታ ብረትና በሌሎች የተሰማሩ አምራቾች እየተበራከቱ ነው ብለዋል።

በዚህም በክልሉ 165 አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዳስትሪዎች በተለያዩ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው የማምረት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።

በተለይ አምራች እንዳስትሪው የማምረት አቅማቸውን የማጎልበትና የሚገጥማቸውን ችግር የመቅረፍ ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

"ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ክልላዊ የንቅናቄ መድረክ በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራር አካላትና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026