
ሀረር፤ጥር 12/2017(ኢዜአ):- በሀረሪ ክልል በአንድ ወር ግዜ ውስጥ 13 ሺህ 480 ሊትር ነዳጅ መያዙን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ረምዚ ሱልጣን እንዳሉት፥ በክልሉ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለማስቆም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በተሰራው ስራ በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 13ሺ 480 ሊትር ነዳጅ ከነተጠርጣሪዎቹ መያዙን ጠቁመዋል።
ነዳጁ የተያዘው በኬላዎች ላይ በተደረገ ፍተሻ እንዲሁም ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ በሕገ ወጥ መንገድ በቤት ውስጥ ተከማችቶ የተገኘ መሆኑን ገልጸዋል።

ነዳጅን በበርሜል በህገ ወጥ መንገድ ሲያሸሹ የተደረሰባቸው እና በመኖሪያ ቤታቸው ደብቀው የተገኙ ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
መንግስት ከፍተኛ በጀት መድቦ የሚያስገባው ነዳጅ ለታለመለት አላማ ሊውል ይገባል ያሉት ኮሚሽነሩ፥ በህገወጥ የነዳጅ ግብይት በሚሳተፉ አካላት ላይ በቀጣይም የተጠናከረ ክትትል በማድረግ አስተማሪ የሆነ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቀዋል።
በቀጣይም ሕገ ወጥ ነዳጅን ጨምሮ ሌሎች ሕገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥሉም ኮሚሽነር ረምዚ ሱልጣን ጠቁመዋል።
ማህበረሰብ በአካባቢው ሕገ ወጥ የነዳጅ ግብይትን ሲመለከት በአካባቢው ለሚገኙ የፖሊስ ጽ/ቤት ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አስተላልፈዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026