
ሀረር፤ጥር 12/2017(ኢዜአ):- በሀረሪ ክልል በአንድ ወር ግዜ ውስጥ 13 ሺህ 480 ሊትር ነዳጅ መያዙን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ረምዚ ሱልጣን እንዳሉት፥ በክልሉ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለማስቆም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በተሰራው ስራ በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 13ሺ 480 ሊትር ነዳጅ ከነተጠርጣሪዎቹ መያዙን ጠቁመዋል።
ነዳጁ የተያዘው በኬላዎች ላይ በተደረገ ፍተሻ እንዲሁም ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ በሕገ ወጥ መንገድ በቤት ውስጥ ተከማችቶ የተገኘ መሆኑን ገልጸዋል።

ነዳጅን በበርሜል በህገ ወጥ መንገድ ሲያሸሹ የተደረሰባቸው እና በመኖሪያ ቤታቸው ደብቀው የተገኙ ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
መንግስት ከፍተኛ በጀት መድቦ የሚያስገባው ነዳጅ ለታለመለት አላማ ሊውል ይገባል ያሉት ኮሚሽነሩ፥ በህገወጥ የነዳጅ ግብይት በሚሳተፉ አካላት ላይ በቀጣይም የተጠናከረ ክትትል በማድረግ አስተማሪ የሆነ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቀዋል።
በቀጣይም ሕገ ወጥ ነዳጅን ጨምሮ ሌሎች ሕገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥሉም ኮሚሽነር ረምዚ ሱልጣን ጠቁመዋል።
ማህበረሰብ በአካባቢው ሕገ ወጥ የነዳጅ ግብይትን ሲመለከት በአካባቢው ለሚገኙ የፖሊስ ጽ/ቤት ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025