
አዳማ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ750 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሮችና ለማህበራት መሰራጨቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።

በቢሮው የእንስሳት ሀብት ልማት ዳይሬክተር አቶ ደምሴ ኩምሣ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በክልሉ የማር ልማት እንሼቲቭ ተቀርጾ ባለፉት ሶስት ዓመታት ሲሰራ ቆይቷል።
ዘንድሮ በክልሉ የማር ምርትን ለማሳደግ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎ ለማሰራጨት ታቅዶ ባለፉት ስድስት ወራት ከ750 ሺህ በላይ መሰራጨቱን ተናግረዋል።
ኢንሼቲቩ በምዕራብ ኦሮሚያ በተለይ በጂማ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉ አባቦር፣ ምዕራብና ምስራቅ ወለጋ፣ ቄሌም ወለጋና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋን ጨምሮ በክልሉ 15 ዞኖች እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አሁን ላይ በክልሉ የተለያዩ ዞኖች የማር ልማት ስራ በአርሶና አርብቶ አደሮች እንዲሁም በወጣቶች እየተከናወነ እንደሆነም ገልጸዋል።
አምና ከ1 ሚሊዮን በላይ ዘመናዊ የንብ ቆፎ ማሰራጨት መቻሉን አስታውሰው፤ ዘንድሮም የንብ ቀፎዎቹ ለአርሶና አብርቶ አደሮች እንዲሁም በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑን አክለዋል።
በክልሉ የማር ምርት በዓመት ሁለት ጊዜ እንደሚሰበሰብ ጠቁመው በዚህ ወቅት የመጀመሪያው በጋ ወቅት የማር ምርት እየተሰበሰበ ሲሆን ቀጣይ ግንቦትና ሰኔ ሁለተኛው ምርት የሚሰበሰብበት መሆኑን ተናግረዋል።
በማር ምርት ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎን ጨምሮ የማር ምርት ማጥለያ፣ ማርና ሰም መለያ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ጥራት ያለው ዘመናዊ ቀፎ ከክልሉ ደን ልማትና ዱር እንስሳት ኢንተርፕራይዝ ጋር በትብብር እየተመረተ መሆኑንም ገልጸዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025