
አዳማ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ750 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሮችና ለማህበራት መሰራጨቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።

በቢሮው የእንስሳት ሀብት ልማት ዳይሬክተር አቶ ደምሴ ኩምሣ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በክልሉ የማር ልማት እንሼቲቭ ተቀርጾ ባለፉት ሶስት ዓመታት ሲሰራ ቆይቷል።
ዘንድሮ በክልሉ የማር ምርትን ለማሳደግ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎ ለማሰራጨት ታቅዶ ባለፉት ስድስት ወራት ከ750 ሺህ በላይ መሰራጨቱን ተናግረዋል።
ኢንሼቲቩ በምዕራብ ኦሮሚያ በተለይ በጂማ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉ አባቦር፣ ምዕራብና ምስራቅ ወለጋ፣ ቄሌም ወለጋና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋን ጨምሮ በክልሉ 15 ዞኖች እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አሁን ላይ በክልሉ የተለያዩ ዞኖች የማር ልማት ስራ በአርሶና አርብቶ አደሮች እንዲሁም በወጣቶች እየተከናወነ እንደሆነም ገልጸዋል።
አምና ከ1 ሚሊዮን በላይ ዘመናዊ የንብ ቆፎ ማሰራጨት መቻሉን አስታውሰው፤ ዘንድሮም የንብ ቀፎዎቹ ለአርሶና አብርቶ አደሮች እንዲሁም በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑን አክለዋል።
በክልሉ የማር ምርት በዓመት ሁለት ጊዜ እንደሚሰበሰብ ጠቁመው በዚህ ወቅት የመጀመሪያው በጋ ወቅት የማር ምርት እየተሰበሰበ ሲሆን ቀጣይ ግንቦትና ሰኔ ሁለተኛው ምርት የሚሰበሰብበት መሆኑን ተናግረዋል።
በማር ምርት ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎን ጨምሮ የማር ምርት ማጥለያ፣ ማርና ሰም መለያ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ጥራት ያለው ዘመናዊ ቀፎ ከክልሉ ደን ልማትና ዱር እንስሳት ኢንተርፕራይዝ ጋር በትብብር እየተመረተ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026