የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ750 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሮችና ለማህበራት ተሰራጭቷል - ግብርና ቢሮ</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ750 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሮችና ለማህበራት መሰራጨቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።


በቢሮው የእንስሳት ሀብት ልማት ዳይሬክተር አቶ ደምሴ ኩምሣ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በክልሉ የማር ልማት እንሼቲቭ ተቀርጾ ባለፉት ሶስት ዓመታት ሲሰራ ቆይቷል።

ዘንድሮ በክልሉ የማር ምርትን ለማሳደግ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎ ለማሰራጨት ታቅዶ ባለፉት ስድስት ወራት ከ750 ሺህ በላይ መሰራጨቱን ተናግረዋል።

ኢንሼቲቩ በምዕራብ ኦሮሚያ በተለይ በጂማ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉ አባቦር፣ ምዕራብና ምስራቅ ወለጋ፣ ቄሌም ወለጋና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋን ጨምሮ በክልሉ 15 ዞኖች እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አሁን ላይ በክልሉ የተለያዩ ዞኖች የማር ልማት ስራ በአርሶና አርብቶ አደሮች እንዲሁም በወጣቶች እየተከናወነ እንደሆነም ገልጸዋል።

አምና ከ1 ሚሊዮን በላይ ዘመናዊ የንብ ቆፎ ማሰራጨት መቻሉን አስታውሰው፤ ዘንድሮም የንብ ቀፎዎቹ ለአርሶና አብርቶ አደሮች እንዲሁም በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑን አክለዋል።

በክልሉ የማር ምርት በዓመት ሁለት ጊዜ እንደሚሰበሰብ ጠቁመው በዚህ ወቅት የመጀመሪያው በጋ ወቅት የማር ምርት እየተሰበሰበ ሲሆን ቀጣይ ግንቦትና ሰኔ ሁለተኛው ምርት የሚሰበሰብበት መሆኑን ተናግረዋል።

በማር ምርት ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎን ጨምሮ የማር ምርት ማጥለያ፣ ማርና ሰም መለያ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ጥራት ያለው ዘመናዊ ቀፎ ከክልሉ ደን ልማትና ዱር እንስሳት ኢንተርፕራይዝ ጋር በትብብር እየተመረተ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026