ባሕር ዳር፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ ባሕር ዳር ከተማን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ባለሀብቶች በሰላም ማስጠበቅ እና ልማት ላይ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ የከተማዋ አስተዳደሩ ጥሪ አቀረበ።
በባሕር ዳር ከተማ ልማትና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።
የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፤ ከተማ አስተዳደሩ ከወትሮው በተለዬ ከተማዋን ለማልማት እየሰራ ነው።
በዚህም የከተማዋን ሰላምና ነዋሪዎችን ደህንነት ከማረጋገጥ በተጓዳኝ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች እየተቀላጠፉ ነው ብለዋል።
ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ ስማርት ሲቲ፣ የዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል።
ትውልድ ተሻጋሪ ፋይዳ ያለው የከተማዋ ኮሪደር ልማትም ዘላቂና ምቹ የኑሮና የስራ ከተማ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑንም እንዲሁ።
ሁሉን አቀፍ የከተማ ልማት ጥረቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ባለሃብቱ የሚጠበቅበትን ወሳኝ ሚና በመረዳት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ከተሳታፊ ባለሃብቶች መካከል አቶ እንግዳው ወርቁና አቶ ማስተዋል አያልነህ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ ምቹና ዘመናዊ ከተማ ግንባታ ፕሮጀክቶችን አድንቀዋል።
በመሆኑም የመንግስትን ጥረት በመደገፍ ከተማን ለኢንቨስመንት ተወዳዳሪ እንድትሆን በባለቤትነት ስሜት እንደሚደግፉ አረጋግጠዋል።
በከተማዋ የተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶችን መገብኘታቸውን ገልጸው፤ የልማት ስራዎችን ከመጠበቅና ከመንከባከብ ባሻገር አዳዲስ የልማት ስራዎችን በመደገፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025