
ባሕር ዳር፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ ባሕር ዳር ከተማን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ባለሀብቶች በሰላም ማስጠበቅ እና ልማት ላይ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ የከተማዋ አስተዳደሩ ጥሪ አቀረበ።
በባሕር ዳር ከተማ ልማትና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።
የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፤ ከተማ አስተዳደሩ ከወትሮው በተለዬ ከተማዋን ለማልማት እየሰራ ነው።
በዚህም የከተማዋን ሰላምና ነዋሪዎችን ደህንነት ከማረጋገጥ በተጓዳኝ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች እየተቀላጠፉ ነው ብለዋል።
ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ ስማርት ሲቲ፣ የዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል።
ትውልድ ተሻጋሪ ፋይዳ ያለው የከተማዋ ኮሪደር ልማትም ዘላቂና ምቹ የኑሮና የስራ ከተማ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑንም እንዲሁ።
ሁሉን አቀፍ የከተማ ልማት ጥረቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ባለሃብቱ የሚጠበቅበትን ወሳኝ ሚና በመረዳት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ከተሳታፊ ባለሃብቶች መካከል አቶ እንግዳው ወርቁና አቶ ማስተዋል አያልነህ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ ምቹና ዘመናዊ ከተማ ግንባታ ፕሮጀክቶችን አድንቀዋል።
በመሆኑም የመንግስትን ጥረት በመደገፍ ከተማን ለኢንቨስመንት ተወዳዳሪ እንድትሆን በባለቤትነት ስሜት እንደሚደግፉ አረጋግጠዋል።
በከተማዋ የተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶችን መገብኘታቸውን ገልጸው፤ የልማት ስራዎችን ከመጠበቅና ከመንከባከብ ባሻገር አዳዲስ የልማት ስራዎችን በመደገፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026