
ባሕር ዳር፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ ባሕር ዳር ከተማን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ባለሀብቶች በሰላም ማስጠበቅ እና ልማት ላይ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ የከተማዋ አስተዳደሩ ጥሪ አቀረበ።
በባሕር ዳር ከተማ ልማትና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።
የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፤ ከተማ አስተዳደሩ ከወትሮው በተለዬ ከተማዋን ለማልማት እየሰራ ነው።
በዚህም የከተማዋን ሰላምና ነዋሪዎችን ደህንነት ከማረጋገጥ በተጓዳኝ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች እየተቀላጠፉ ነው ብለዋል።
ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ ስማርት ሲቲ፣ የዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል።
ትውልድ ተሻጋሪ ፋይዳ ያለው የከተማዋ ኮሪደር ልማትም ዘላቂና ምቹ የኑሮና የስራ ከተማ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑንም እንዲሁ።
ሁሉን አቀፍ የከተማ ልማት ጥረቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ባለሃብቱ የሚጠበቅበትን ወሳኝ ሚና በመረዳት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ከተሳታፊ ባለሃብቶች መካከል አቶ እንግዳው ወርቁና አቶ ማስተዋል አያልነህ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ ምቹና ዘመናዊ ከተማ ግንባታ ፕሮጀክቶችን አድንቀዋል።
በመሆኑም የመንግስትን ጥረት በመደገፍ ከተማን ለኢንቨስመንት ተወዳዳሪ እንድትሆን በባለቤትነት ስሜት እንደሚደግፉ አረጋግጠዋል።
በከተማዋ የተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶችን መገብኘታቸውን ገልጸው፤ የልማት ስራዎችን ከመጠበቅና ከመንከባከብ ባሻገር አዳዲስ የልማት ስራዎችን በመደገፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026