
ደሴ ኢዜአ ጥር 28/2017-- በደቡብ ወሎ ዞን በዘንድሮው የበልግ ወቅት ከ104 ሺህ 600 በላይ ሄክታር መሬት እየታረሰ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ አርሶ አደሩ የሰብል ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ በትኩረት እየተሰራ ነው።
በዘንድሮው የበልግ ወቅት ከ104 ሺህ 600 ሄክታር የሚበልጥ መሬት እየታረሰ ሲሆን፤በሚቀጥለው ወር የዘር ስራ እንደሚጀመር ተናግረዋል፡፡

በበልግ ወቅቱ ከሚለማው መሬት ከሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት መታቀዱንም ነው የተናገሩት።
ምርታማነትን ለማሳደግም ከሁለት ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያን ጨምሮ የፋብሪካ ማዳበሪያም ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል።
በዞኑ ለጋምቦ ወረዳ የቀበሌ 14 ነዋሪ አርሶ አደር በላይ አህመድ፤ በአንድ ሄክታር ተኩል መሬት ላይ ገብስ፣ ስንዴና ጤፍ ለማልማት የእርሻ ሥራ አጠናቀዋል፡፡
ከሚያለሙት መሬትም ከ30 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠብቁ ጠቁመው፤ ባለፈው ዓመት ከዚህ መሬት 26 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን አስታውሰዋል።
የበልግ ዝናብ ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን የተናገሩት ሌላው የደሴ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደር ከድር ሙሄው ናቸው።
በዘንድሮ የበልግ ወቅትም አንድ ሄክታር መሬት በገብስ፣ ስንዴና ባቄላ ዘር ለመሸፈን የእርሻ ስራ በማጠናቀቅ የዝናቡን መጣል እየተጠባበቁ ይገኛል፡፡

ከልማቱ ከ20 ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡
በዞኑ ባለፈው ዓመት በበልግ ወቅት ከለማው 105 ሺህ ሄክታር መሬት 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከመምሪያው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026