የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ዩኒቨርሲቲው የምርምር ውጤቶቹን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ ነው</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አክሱም፤ ጥር 29/2017 (ኢዜአ)፦ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በምርምር ያወጣቸውን የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ መሆኑን ገለጸ።

በዩኒቨርሲቲው የመካኒካልና ኢንዳስትሪያል ምህንድስና ትምህርት ከፍል መምህር ገብረሚካኤል ገብረማርያም ለኢዜአ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር እያወጣ ነው።

ለአብነትም "በዲናሞ" እና በሰው ሃይል ጉልበት የሚሰሩ የሰብል መዝርያ፣ ማጨጃና መውቂያ ማሽኖችን ጠቅሰዋል።

ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የተሰሩት የግብርና ቴክኖሎጂዎች ገብስ፣ ሰንዴና ሌሎች ሰብሎችን በመስመር መዝራት፣ ማጨድ፣ መሰብሰብና መውቃት የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሌላው በትምህርት ክፍሉ መምህር ገብረሚካኤል ገብረመድህን በበኩላቸው የወዳደቁ ብረታ ብረቶችን በመጠቀም በአንድ ጊዜ በአራት መስመሮች ሰብልን መዝራት የሚያስችል ማሽን መስራታቸውን ገልጸዋል።

ቴክኖሎጂው ዘርን ከብክነት ከመከላከል አልፎ የአርሶ አደሩን ጉልበትና የሥራ ጊዜን የመቆጠብ አቅም እንዳለው ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው የግብርና ቴክኖሎጂዎቹን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ መሆኑን ምሁራኑ አስታውቀዋል።

ኢዜአ ካነጋገራቸው አርሶ አደሮች መካከል ተክለወይኒ ገብረስላሴ፣ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የሰራው ዘመናዊ ማጭድ በጠባብ የእርሻ ማሳ ሰብልን በአጭር ግዜ ለመሰብሰብ ምቹ መሆኑን ገልጸዋል።

"በዲናሞ" የሚሰራ የማረሻ ማሽን የሰውን ጉልበት እንደሚቆጥብ በተግባር ማረጋገጣቸውን የተናገሩት ደግሞ አርሶ አደር ሃፍተወልድ መኮንን ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.