
አክሱም፤ ጥር 29/2017 (ኢዜአ)፦ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በምርምር ያወጣቸውን የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ መሆኑን ገለጸ።
በዩኒቨርሲቲው የመካኒካልና ኢንዳስትሪያል ምህንድስና ትምህርት ከፍል መምህር ገብረሚካኤል ገብረማርያም ለኢዜአ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር እያወጣ ነው።
ለአብነትም "በዲናሞ" እና በሰው ሃይል ጉልበት የሚሰሩ የሰብል መዝርያ፣ ማጨጃና መውቂያ ማሽኖችን ጠቅሰዋል።
ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የተሰሩት የግብርና ቴክኖሎጂዎች ገብስ፣ ሰንዴና ሌሎች ሰብሎችን በመስመር መዝራት፣ ማጨድ፣ መሰብሰብና መውቃት የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ሌላው በትምህርት ክፍሉ መምህር ገብረሚካኤል ገብረመድህን በበኩላቸው የወዳደቁ ብረታ ብረቶችን በመጠቀም በአንድ ጊዜ በአራት መስመሮች ሰብልን መዝራት የሚያስችል ማሽን መስራታቸውን ገልጸዋል።
ቴክኖሎጂው ዘርን ከብክነት ከመከላከል አልፎ የአርሶ አደሩን ጉልበትና የሥራ ጊዜን የመቆጠብ አቅም እንዳለው ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው የግብርና ቴክኖሎጂዎቹን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ መሆኑን ምሁራኑ አስታውቀዋል።
ኢዜአ ካነጋገራቸው አርሶ አደሮች መካከል ተክለወይኒ ገብረስላሴ፣ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የሰራው ዘመናዊ ማጭድ በጠባብ የእርሻ ማሳ ሰብልን በአጭር ግዜ ለመሰብሰብ ምቹ መሆኑን ገልጸዋል።
"በዲናሞ" የሚሰራ የማረሻ ማሽን የሰውን ጉልበት እንደሚቆጥብ በተግባር ማረጋገጣቸውን የተናገሩት ደግሞ አርሶ አደር ሃፍተወልድ መኮንን ናቸው።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025