
አክሱም፤ ጥር 29/2017 (ኢዜአ)፦ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በምርምር ያወጣቸውን የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ መሆኑን ገለጸ።
በዩኒቨርሲቲው የመካኒካልና ኢንዳስትሪያል ምህንድስና ትምህርት ከፍል መምህር ገብረሚካኤል ገብረማርያም ለኢዜአ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር እያወጣ ነው።
ለአብነትም "በዲናሞ" እና በሰው ሃይል ጉልበት የሚሰሩ የሰብል መዝርያ፣ ማጨጃና መውቂያ ማሽኖችን ጠቅሰዋል።
ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የተሰሩት የግብርና ቴክኖሎጂዎች ገብስ፣ ሰንዴና ሌሎች ሰብሎችን በመስመር መዝራት፣ ማጨድ፣ መሰብሰብና መውቃት የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ሌላው በትምህርት ክፍሉ መምህር ገብረሚካኤል ገብረመድህን በበኩላቸው የወዳደቁ ብረታ ብረቶችን በመጠቀም በአንድ ጊዜ በአራት መስመሮች ሰብልን መዝራት የሚያስችል ማሽን መስራታቸውን ገልጸዋል።
ቴክኖሎጂው ዘርን ከብክነት ከመከላከል አልፎ የአርሶ አደሩን ጉልበትና የሥራ ጊዜን የመቆጠብ አቅም እንዳለው ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው የግብርና ቴክኖሎጂዎቹን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ መሆኑን ምሁራኑ አስታውቀዋል።
ኢዜአ ካነጋገራቸው አርሶ አደሮች መካከል ተክለወይኒ ገብረስላሴ፣ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የሰራው ዘመናዊ ማጭድ በጠባብ የእርሻ ማሳ ሰብልን በአጭር ግዜ ለመሰብሰብ ምቹ መሆኑን ገልጸዋል።
"በዲናሞ" የሚሰራ የማረሻ ማሽን የሰውን ጉልበት እንደሚቆጥብ በተግባር ማረጋገጣቸውን የተናገሩት ደግሞ አርሶ አደር ሃፍተወልድ መኮንን ናቸው።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026