
አክሱም፤ ጥር 29/2017 (ኢዜአ)፦ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በምርምር ያወጣቸውን የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ መሆኑን ገለጸ።
በዩኒቨርሲቲው የመካኒካልና ኢንዳስትሪያል ምህንድስና ትምህርት ከፍል መምህር ገብረሚካኤል ገብረማርያም ለኢዜአ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር እያወጣ ነው።
ለአብነትም "በዲናሞ" እና በሰው ሃይል ጉልበት የሚሰሩ የሰብል መዝርያ፣ ማጨጃና መውቂያ ማሽኖችን ጠቅሰዋል።
ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የተሰሩት የግብርና ቴክኖሎጂዎች ገብስ፣ ሰንዴና ሌሎች ሰብሎችን በመስመር መዝራት፣ ማጨድ፣ መሰብሰብና መውቃት የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ሌላው በትምህርት ክፍሉ መምህር ገብረሚካኤል ገብረመድህን በበኩላቸው የወዳደቁ ብረታ ብረቶችን በመጠቀም በአንድ ጊዜ በአራት መስመሮች ሰብልን መዝራት የሚያስችል ማሽን መስራታቸውን ገልጸዋል።
ቴክኖሎጂው ዘርን ከብክነት ከመከላከል አልፎ የአርሶ አደሩን ጉልበትና የሥራ ጊዜን የመቆጠብ አቅም እንዳለው ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው የግብርና ቴክኖሎጂዎቹን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ መሆኑን ምሁራኑ አስታውቀዋል።
ኢዜአ ካነጋገራቸው አርሶ አደሮች መካከል ተክለወይኒ ገብረስላሴ፣ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የሰራው ዘመናዊ ማጭድ በጠባብ የእርሻ ማሳ ሰብልን በአጭር ግዜ ለመሰብሰብ ምቹ መሆኑን ገልጸዋል።
"በዲናሞ" የሚሰራ የማረሻ ማሽን የሰውን ጉልበት እንደሚቆጥብ በተግባር ማረጋገጣቸውን የተናገሩት ደግሞ አርሶ አደር ሃፍተወልድ መኮንን ናቸው።
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...
Jul 13, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...
Jul 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 7, 2026