የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>አቶ መስፍን ጣሰው በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ አህጉራዊ የአመራርነት ሽልማት አገኙ</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው “Leadership in Connecting Africa through Transport Award” የተሰኘ አህጉራዊ ሽልማት አግኝተዋል።

በአፍሪካ አህጉር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና ላይ ያተኮረ ዓመታዊ የ“2025 የአፍሪካ ፕሮስፔሪቲ ዲያሎግ” በጋና አክራ ተካሂዷል።

በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት በማገናኘት ረገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየተጫወተ ላለው ሚና ላሳዩት የላቀ የአመራርነት ሚና የ“Leadership in Connecting Africa through Transport Award” ተሸላሚ ሆነዋል።

ሽልማቱ አፍሪካን እርስ በእርስ በማገናኘት ቁርጠኛ የአመራርነት አስተዋፅዖ ላበረከቱ ግለሰቦች ዕውቅና የሚሰጥበት መሆኑን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የ“2025 የአፍሪካ ፕሮስፔሪቲ ዲያሎግ” ላይ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የታላላቅ አህጉር ዓቀፍ የንግድ ተቋማት መሪዎች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.