
አዲስ አበባ፤ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦በተያዘው ዓመት አምስት የሚደርሱ ኩባንያዎችን ወደ አክሲዮን ገበያው ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጥላሁን እስማኤል(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የተለያዩ የንግድ አይነቶችን ታሳቢ በማድረግ ሶስት ልዩ ልዩ የገበያ አይነቶችን የሚያቀርብ ነው፡፡
እነርሱም የአክሲዮን ገበያ፣ የዕዳ ሰነድ ገበያ እና የአማራጭ ገበያ ናቸው፡፡
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጥላሁን እስማኤል(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ተቋሙ ዓለም ላይ ካሉ የካፒታል ገበያ ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያስችለውን የሕግ ማዕቀፍና አስፈላጊ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን አሟልቶ ወደ ሥራ ገብቷል።
አሁን ላይ አንድ የግል ባንክ በገበያው ለመሳተፍ መመዝገቡን ጠቅሰው፤ በቀጣይም ኢትዮ - ቴሌኮምን ጨምሮ አምስት ኩባንያዎችን እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን ይቀላቀላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።
በገበያው የተለያዩ የፋይናንስ ውጤቶችንም የማስተዋወቅ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸው፤ ይህንንም ተከትሎ የሀገር ውስጥና የውጭ ኩባንያዎች ለማሳተፍ ፍላጎት እያሳዩ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም በኢትዮጵያ በባንኮች መካከል ያለው የገንዘብ ገበያና የዕዳ ሰነድ ገበያው ፍላጎቱ እንዲጨምር ማድረጉን አስረድተዋል።
በቀጣይ ስድስት ዓመታትም 50 የሚሆኑ ኩባንያዎችን ወደ ገበያው በመቀላቀል የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ላይ ካሉ የተሻሉ ተቋማት ተርታ የማሰለፍ እቅድ መኖሩን አስረድተዋል።
ይህንንም ርዕይ እውን ለማድረግ የቁጠባ ባህላቸው ያደገ እንዲሁም ሀብት በማሰባሰብ ኢንቨስት የሚያደርጉ ተቋማት የተከማቹባቸው አገራትን ትኩረት ያደረገ ገበያውን የማስተዋወቅ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ለአብነትም ደቡብ አፍሪካ፣ ለንደን፣ ዱባይና ኒውዮርክ ላይ ትኩረት ያደረጉ ገበያውን የማስተዋወቅ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ከካዛብላንካ፣ ከናይሮቢና ከናይጄሪያ የካፒታል ገበያ ጋር አጋርነት እንዳለው ገልጸው፣ የአፍሪካና የምስራቅ አፍሪካ የካፒታል ገበያ ማኅበር አባል መሆኑን ጠቅሰዋል።
ይህም የተቋሙን ውጤታማነትና ተወዳዳሪነት እንዲሁም በፈጠራ የታከለ ገበያ ለመገንባት አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ገበያው ከዓለም አቀፍ የዘርፉ ኢንዱስትሪ ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያስችል አጠቃላይ የካፒታል ገበያን ሥነ-ምህዳር የማስተካከል ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...
Jul 13, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...
Jul 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 7, 2026