አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በድሮን ታክቲካል አጠቃቀም ላይ ያሰለጠናቸውን የፖሊስ እና የሪፐብሊካን ጋርድ የድሮን ባለሙያዎችን አስመርቋል።
ስልጠናው የሰጡት የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የዱባይ ፖሊስ ኦፊሰሮች ናቸው።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ለሚኒስቴሩ እና ለዱባይ ፖሊስ ምስጋና አቅርበዋል።
ስልጠናው የፖሊስ መኮንኖችን ሙያዊ ኃላፊነት ለመወጣት ያላቸውን አቅም እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ በሚካሄደው የ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የዝግጅቱን ደህንነት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።
ኮሚሽነር ጀነራሉ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ እና የሪፐብሊካን ጋርድ የድሮን ባለሙያዎች ያገኙትን ዕውቀት ለተፈለገው ዓላማ በማዋል በከፍተኛ ሙያዊ ዲስፕሊን በብቃት እንዲወጡ አሳስበዋል።
በተጨማሪም የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የዱባይ ፖሊስ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ላደረጉት ሙያዊና የሎጂስቲክስ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ድጋፉ የፖሊስ ሰራዊቱ ተልዕኮውን በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጽም ከፍተኛ ሚና አንዳለው መግለጻቸውን ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025