
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በድሮን ታክቲካል አጠቃቀም ላይ ያሰለጠናቸውን የፖሊስ እና የሪፐብሊካን ጋርድ የድሮን ባለሙያዎችን አስመርቋል።
ስልጠናው የሰጡት የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የዱባይ ፖሊስ ኦፊሰሮች ናቸው።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ለሚኒስቴሩ እና ለዱባይ ፖሊስ ምስጋና አቅርበዋል።
ስልጠናው የፖሊስ መኮንኖችን ሙያዊ ኃላፊነት ለመወጣት ያላቸውን አቅም እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ በሚካሄደው የ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የዝግጅቱን ደህንነት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።
ኮሚሽነር ጀነራሉ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ እና የሪፐብሊካን ጋርድ የድሮን ባለሙያዎች ያገኙትን ዕውቀት ለተፈለገው ዓላማ በማዋል በከፍተኛ ሙያዊ ዲስፕሊን በብቃት እንዲወጡ አሳስበዋል።

በተጨማሪም የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የዱባይ ፖሊስ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ላደረጉት ሙያዊና የሎጂስቲክስ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ድጋፉ የፖሊስ ሰራዊቱ ተልዕኮውን በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጽም ከፍተኛ ሚና አንዳለው መግለጻቸውን ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025