የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>የከተማዋን ገጽታ የቀየሩና የህዝቡን የልማት ጥያቄ የመለሱ ሰፋፊ ስራዎች ተከናውነዋል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ</p>

Feb 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት የከተማዋን ገጽታ የቀየሩና የህዝቡን የልማት ጥያቄ የመለሱ ሰፋፊ ስራዎች መከናወናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።


አስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት የመንግስት እና የፓርቲ የስድስት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ማካሄድ ጀምሯል።


በዚሁ ወቅት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ባለፉት ስድስት ወራት በሁሉም ዘርፎች አመርቂ አፈጻጸሞች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።


በአስተዳደሩ የዕቅድ አፈጻጸም አጠቃላይ ደረጃ 90 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፥አፈጻጸሙ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡


ከህዝቡ በተሰበሰበው ገቢ ህዝቡን ተጠቃሚ ከማድረግ እና ዘላቂ ልማትን ከማረጋገጥ አኳያ አርዓያ የሚሆኑ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።


ከዚህ አንጻር በመዲናዋ ባለፉት ስድስት ወራት ዘላቂ ልማትንና የህዝብ ተጠቃሚነትን ያረጋገጡ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡


አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹና ውብ የሆነች ከተማ ለማድረግ በመልሶ ግንባታ እና በመሠረተ ልማት ማስፋፋት የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውንም ከንቲባ አዳነች ተናግረዋል።


የከተማዋን ዘላቂ ልማት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማን ዘላቂ ሰላም ማስጠበቅ መቻሉን ተከትሎ የቱሪዝም ፍሰቱ መጨመሩን ጠቁመዋል፡፡


በስድስት ወራቱ የተመዘገቡ አፈጻጸሞችና የተገኙ ውጤቶች ከከተማዋ የልማት ፍላጎት አንጻር በቀጣይ በርካታ ስራዎች እንደሚከናወኑ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡


በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን የተጀመሩ ውጤታማ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ጠቁመዋል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ ፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ አደም ኑሪ ባቀረቡት ሪፖርት፤ የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ እና ከእጅ ንክኪ ነጻ ከማድረግ አንጻር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።


ባለፉት ስድስት ወራት በመዲናዋ 111 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ጠቁመው፤ ለ148 ሺህ 908 ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩንም ተናግረዋል።


የከተማዋን ገጽታ የቀየሩ የህዝቡን ልማት ፍላጎት የመለሱ ሰፋፊ ስራዎች መከናወናቸውን በዚህም ከተማዋ የተሞክሮ ተምሳሌት መሆን መጀመሯንም ጠቁመዋል፡፡


የአስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት የመንግስት እና የፓርቲ የስድስት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን በከተማዋ በተለያየ እርከን የሚገኙ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.