የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>የክልል ምክር ቤት አባላቱ የባሕር ዳር ከተማን የኮሪደር ልማትን እየጎበኙ ነው</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 02/2017(ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ምክር ቤት አባላት የባሕር ዳር ከተማን የኮሪደር ልማት እየጎበኙ ነው።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው የኮሪደር ልማቱን እስከ ሌሊት በመሥራት ከተማዋ ለነዋሪዎች የተመቼች፣ ጽዱ፣ ውብ እና ማራኪ እየኾነች መኾኗን ለጎብኝዎቹ አስረድተዋል።

የወጣቱን ስብዕና መገንቢያ የሚኾኑ የመዝናኛና የቤተ መጻሕፍት ሥፍራዎች መገንባታቸውንም አንስተዋል።

የምክር ቤት አባላቱ የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታም እየቀየረ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ ጣና ሐይቅና ከተማዋን ያስተሳሰረ ሥራ መሠራቱ ለቱሪዝም ልማቱ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማቱ የሥራ ባሕልን መቀየሩን የክልሉ ኮሙኒኬሸን መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.