የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>በኢሉባቦር ዞን የቡና ምርት መጠንና ጥራት በመጨመር ተጠቃሚነትን የማሳደግ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው</p>

Feb 14, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ የቡና ምርት መጠንና ጥራት በመጨመር ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን በኢሉባቦር ዞን ሁሩሙ ወረዳ በቡና እድሳት ስራ ላይ የሚገኙ አርሶ አደሮች ተናገሩ።

በኢሉ ባቦር ዞን የሁሩሙ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ ታምሩ ፍሪሳ ያረጁ እና ምርታማነታቸው የቀነሱ የቡና ተክሎችን እያደሱ መሆኑን ተናግረዋል።


ካላቸው የቡና ማሳ በዚህ ዓመት አንድ ሔክታር ያህሉን በጉንደላ እያደሱ እንደሆነ የገለጹት አቶ ታምሩ፤ የቡና ተክሎቹ ለረዥም ጊዜ በመቆየት ምርታማነታቸው የቀነሱ መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ ዮሴፍ ስለሺ በበኩላቸው ያረጁ የቡና ተክሎችን በአዲስ መተካት ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ጉልህ ድርሻ እንዳለው አንስተው፤ ይህንኑ በባለሙያዎች ታግዘው በመሥራት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሌላኛው የዚሁ ወረዳ ነዋሪ አቶ ታረቀኝ ገለታ እንዳሉት ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የቡና እድሳት ስራውን በኩታ ገጠም እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

ያረጀ ቡና ምርታማነቱ የሚቀንስ በመሆኑ ተጠቃሚ እንደማይሆኑ አክለዋል።


በዞኑ የሁሩሙ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዱቃሃር ሺፋ በወረዳው በ1ሺህ 630 ሔክታር መሬት ላይ የቡና እድሳት ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ያረጀ የቡና ተክል ምርቱ ከመቀነስም በላይ የቡናው ፍሬ መጠንም ትናንሽ እየሆነ ስለሚሄድ ጥራት ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ገልጸዋል።

በመሆኑም የቡና እድሳት ስራ ወሳኝ ስለሆነ በአርሶ አደሮች በንቃት እየተከናወነ ነው ብለዋል።


በኢሉባቦር ዞን በተያዘው ዓመት ከ22ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የሚገኝ ቡናን የማደስ ስራ በመደበኛ ፕሮግራም እና በኩታ ገጠም እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መልካሙ ጫሊ ናቸው።

የቡና ዕድሳት ስራው በጉንደላና በመንቀል የሚከናወን መሆኑን ጠቁመው፤ ከአጠቃላይ እቅዱ 7ሺህ 918 ሔክታር መሬት ላይ ያረጀ ቡና ተነቅሎ በአዲስ የቡና ችግኝ የሚተካ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026