
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና አህጉራዊ የእሴት ሰንሰለቶችን በማዋሃድ ውጤታማ ለውጥ ለማምጣት ትልቅ አቅም እንዳለው በአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር አምባሳደር አልበርት ሙቻንጋ ገለጹ።
ኮሚሽነሩ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በኢንዱስትሪ እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም አጀንዳ 2063ትን ማሳካት የሚያስችሉ አበረታች ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።
በመረጃ ላይ የተመሰረተ ሪፖርቶችን በማውጣት ተስማሚ ፖሊሲዎች እንዲወጡ ጠንካራ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
እንዲሁም የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን ለመመስረት የድርድር ፊርማ ማፅድቅ እና ወደ ስራ እንዲገባ የማመቻቸት ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል።
አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና አህጉራዊ የእሴት ሰንሰለቶችን በማዋሃድ ውጤታማ ለውጥ ለማምጣት ትልቅ አቅም እንዳለው ተናግረዋል።
ይህም በአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን ለማፋጠን የድርጊት መርሃ ግብሩን መተግበር ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቅሰው፤ ለስኬታማነቱ የሚያገለግሉ ተግባራትን ሀገራት ማከናወን እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
በአፍሪካ አህጉራዊ የእሴት ሰንሰለቶች ላይ የካርታ ስራ መሰራቱንና ከፍተኛ አቅም ያላቸው 94 የእሴት ሰንሰለቶች መለየታቸውን ተናግረዋል።
ፋርማሲዩቲካል፣ የምግብ፣ የአልባሳት እና አውቶሞቲቭ ዘርፎች ቢያንስ አምስት የአፍሪካ ሀገራትን የሚያገናኝ የእሴት ሰንስለት መኖሩን ጠቁመዋል።
እያንዳንዱ የእሴት ሰንሰለት ለሴቶች እና ወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር እና ዘላቂ ልማትን በማስተዋወቅ ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑንም አመላክተዋል።
ከአፍሪካ ግቦች ጋር በማጣጣም የጤና፣ የምግብ ዋስትናን ለማሻሻል እና የአፍሪካ አህጉራዊ የነጻ ንግድ ቀጣና ውድድርን በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ተስፋ ሰጪ መሆናቸው መለየቱን ገልጸዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026