የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>የኢንቨስትመንት አስፈፃሚዎች የጋራ የምክክር መድረክ በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

ጅግጅጋ ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ)፡- የፌዴራል ፣የክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈፃሚዎች የምክክር መድረክ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በዚህም የፌዴራል፣ የክልል እና ከተማ አስተዳድሮች የግማሽ በጀት ዓመቱ የስራ አፈጻጸም እንደሚገመግም ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል።


በተለይም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እያከናወነ የሚገኘውን መጠነ ሰፊ ስራዎች ወደተሻለ ደረጃ ማድረስ እና ዘርፉ በሀገራዊ ዕድገት ላይ የራሱን አበርክቶ በማከል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማሳደግም ላይ ምክክር እንደሚካሄድ ተመልክቷል።

ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው የምክክር መድረክ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሸነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማንን ጨምሮ ሌሎችም የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨትመንትና የኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.