ጅግጅጋ ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ)፡- የፌዴራል ፣የክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈፃሚዎች የምክክር መድረክ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በዚህም የፌዴራል፣ የክልል እና ከተማ አስተዳድሮች የግማሽ በጀት ዓመቱ የስራ አፈጻጸም እንደሚገመግም ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል።
በተለይም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እያከናወነ የሚገኘውን መጠነ ሰፊ ስራዎች ወደተሻለ ደረጃ ማድረስ እና ዘርፉ በሀገራዊ ዕድገት ላይ የራሱን አበርክቶ በማከል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማሳደግም ላይ ምክክር እንደሚካሄድ ተመልክቷል።
ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው የምክክር መድረክ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሸነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማንን ጨምሮ ሌሎችም የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨትመንትና የኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025