የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ከ20 በላይ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች ነው-ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ከ20 በላይ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ፡፡

የአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ጉባዔ የአባል አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የልማት አጋሮች በተገኙበት ተካሒዷል፡፡

ጉባዔውን በተመለከተ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

አቶ አሕመድ ሽዴ በመግለጫቸው፥ የአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢንሼቲቭ በመሰረተ ልማት፣ በጤና፣ በድርቅ ቅነሳና በሌሎች ዘርፎች ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሶማሊያን፣ ጅቡቲን፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚይዝ አመላክተዋል፡፡

በጉባዔው ባለፉት አመታት ከአጋር አካላት የተሰበሰበው የሐብት መጠንና የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ተገምግሟል ብለዋል።

እስካሁን ድረስ 9 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር መሰብሰቡንና በአፈጻጸም ደረጃም ኢትዮጵያ በተሻለ ሁኔታ እንደምትገኝ በጉባዔው መገምገሙን አመላክተዋል፡፡

በዚህም ከተሰበሰበው ሀብት ኢትዮጵያ 3 ቢሊዮን ዶላር እንድታገኝ አስችሏታል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ከ20 በላይ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል።

እየተከናወኑ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል የአዲስ አበባ- ጅቡቲ፣ የአዲስ አበባ -በርበራ፣ የመኢሶን -ድሬዳዋ ያሉ የመንገድ፣ የመብራትና የሪጅናል ዲጅታል መሰረተ ልማቶችን ለአብነት አንስተዋል፡፡

በኢኒሼቲቩ የሚገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች ከአንድ ሀገር በላይ ጠቀሜታ ያላቸው መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡

ጉባዔው በቀጣይ የልማት ትስስሩን በማጠናከር በትምህርትና በሉሎች ዘርፎች ያለውን የአባል ሀገራት ትብብር ለማጠናከር አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጸዋል፡፡

ለዚህም ተጨማሪ ሐብት የማሰባሰብ ስራ ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025