
አዲስ አበባ ፤የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ከ20 በላይ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ፡፡
የአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ጉባዔ የአባል አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የልማት አጋሮች በተገኙበት ተካሒዷል፡፡
ጉባዔውን በተመለከተ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
አቶ አሕመድ ሽዴ በመግለጫቸው፥ የአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢንሼቲቭ በመሰረተ ልማት፣ በጤና፣ በድርቅ ቅነሳና በሌሎች ዘርፎች ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሶማሊያን፣ ጅቡቲን፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚይዝ አመላክተዋል፡፡
በጉባዔው ባለፉት አመታት ከአጋር አካላት የተሰበሰበው የሐብት መጠንና የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ተገምግሟል ብለዋል።
እስካሁን ድረስ 9 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር መሰብሰቡንና በአፈጻጸም ደረጃም ኢትዮጵያ በተሻለ ሁኔታ እንደምትገኝ በጉባዔው መገምገሙን አመላክተዋል፡፡
በዚህም ከተሰበሰበው ሀብት ኢትዮጵያ 3 ቢሊዮን ዶላር እንድታገኝ አስችሏታል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ከ20 በላይ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል።
እየተከናወኑ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል የአዲስ አበባ- ጅቡቲ፣ የአዲስ አበባ -በርበራ፣ የመኢሶን -ድሬዳዋ ያሉ የመንገድ፣ የመብራትና የሪጅናል ዲጅታል መሰረተ ልማቶችን ለአብነት አንስተዋል፡፡
በኢኒሼቲቩ የሚገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች ከአንድ ሀገር በላይ ጠቀሜታ ያላቸው መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡
ጉባዔው በቀጣይ የልማት ትስስሩን በማጠናከር በትምህርትና በሉሎች ዘርፎች ያለውን የአባል ሀገራት ትብብር ለማጠናከር አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጸዋል፡፡
ለዚህም ተጨማሪ ሐብት የማሰባሰብ ስራ ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026