የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ከ20 በላይ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች ነው-ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ከ20 በላይ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ፡፡

የአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ጉባዔ የአባል አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የልማት አጋሮች በተገኙበት ተካሒዷል፡፡

ጉባዔውን በተመለከተ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

አቶ አሕመድ ሽዴ በመግለጫቸው፥ የአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢንሼቲቭ በመሰረተ ልማት፣ በጤና፣ በድርቅ ቅነሳና በሌሎች ዘርፎች ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሶማሊያን፣ ጅቡቲን፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚይዝ አመላክተዋል፡፡

በጉባዔው ባለፉት አመታት ከአጋር አካላት የተሰበሰበው የሐብት መጠንና የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ተገምግሟል ብለዋል።

እስካሁን ድረስ 9 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር መሰብሰቡንና በአፈጻጸም ደረጃም ኢትዮጵያ በተሻለ ሁኔታ እንደምትገኝ በጉባዔው መገምገሙን አመላክተዋል፡፡

በዚህም ከተሰበሰበው ሀብት ኢትዮጵያ 3 ቢሊዮን ዶላር እንድታገኝ አስችሏታል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የልማት ኢኒሼቲቭ ከ20 በላይ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል።

እየተከናወኑ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል የአዲስ አበባ- ጅቡቲ፣ የአዲስ አበባ -በርበራ፣ የመኢሶን -ድሬዳዋ ያሉ የመንገድ፣ የመብራትና የሪጅናል ዲጅታል መሰረተ ልማቶችን ለአብነት አንስተዋል፡፡

በኢኒሼቲቩ የሚገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች ከአንድ ሀገር በላይ ጠቀሜታ ያላቸው መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡

ጉባዔው በቀጣይ የልማት ትስስሩን በማጠናከር በትምህርትና በሉሎች ዘርፎች ያለውን የአባል ሀገራት ትብብር ለማጠናከር አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጸዋል፡፡

ለዚህም ተጨማሪ ሐብት የማሰባሰብ ስራ ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026