የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>በትግራይ ክልል በ2017/18 የምርት ዘመን የተሻለ ምርት ማግኘት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡- በትግራይ ክልል በ2017/18 የምርት ዘመን የተሻለ ምርት ማግኘት የሚያስችሉ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮ ኃላፊው እያሱ አብርሃ(ዶ/ር) እንደገለፁት፤ እየተካሄዱ ካሉ የዝግጅት ስራዎች መካከል እርጥበትን ማከማቸት የሚያስችለው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አንዱ ነው።

የዝናብ ውሃን ወደ ከርሰ ምድር በማስረግ የእርሻ መሬት እርጥበትን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀው በተለይም ከሚቀጥለው መጋቢት ወር ጀምሮ በማሳ ላይ ትኩረት በማድረግ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው በስፋት ይከናወናል ብለዋል።


እንዲሁም ለመጪው ክረምት የሚያስፈልግ አንድ ሚሊዮን ኩንታል ዘመናዊ የአፈር ማዳበሪያ ከወዲሁ እየተጓጓዘ መሆኑን አመልክተዋል።

በክልሉ ለምርት ዘመኑ 150 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር እንደሚያስፈልግ የገለጹት የቢሮ ኃላፊው ባለፈው ዓመት የክልሉ አርሶ አደር በራሱ አቅም 55 ሺህ ኩንታል እንዲያባዛ በመደረጉ እጥረቱን እንደሚያቃልለው አብራርተዋል።

በልግ አብቃይ ከሆኑ ወረዳዎች በተጨማሪ አርሶ አደሮች ማሳቸውን በአዝመራ ለመሸፈን እያከናወኑ መሆኑን በመግለፅ እየዘነበ ያለውን ዝናብ ወደ ማሳ የማስገባት ስራ በስፋት እየተካሄደ ነው ብለዋል።

በመጪው ክረምት ከ800 ሺህ በላይ ሄክታር መሬትን በተለያዩ አዝርእቶች በመሸፈን 24 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ቢሮ ኃላፊው አብራርተዋል።

በ2016/17 የምርት ዘመን ከክልሉ 13 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ቢሮው መግለፁ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.