
መቀሌ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡- በትግራይ ክልል በ2017/18 የምርት ዘመን የተሻለ ምርት ማግኘት የሚያስችሉ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮ ኃላፊው እያሱ አብርሃ(ዶ/ር) እንደገለፁት፤ እየተካሄዱ ካሉ የዝግጅት ስራዎች መካከል እርጥበትን ማከማቸት የሚያስችለው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አንዱ ነው።
የዝናብ ውሃን ወደ ከርሰ ምድር በማስረግ የእርሻ መሬት እርጥበትን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀው በተለይም ከሚቀጥለው መጋቢት ወር ጀምሮ በማሳ ላይ ትኩረት በማድረግ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው በስፋት ይከናወናል ብለዋል።

እንዲሁም ለመጪው ክረምት የሚያስፈልግ አንድ ሚሊዮን ኩንታል ዘመናዊ የአፈር ማዳበሪያ ከወዲሁ እየተጓጓዘ መሆኑን አመልክተዋል።
በክልሉ ለምርት ዘመኑ 150 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር እንደሚያስፈልግ የገለጹት የቢሮ ኃላፊው ባለፈው ዓመት የክልሉ አርሶ አደር በራሱ አቅም 55 ሺህ ኩንታል እንዲያባዛ በመደረጉ እጥረቱን እንደሚያቃልለው አብራርተዋል።
በልግ አብቃይ ከሆኑ ወረዳዎች በተጨማሪ አርሶ አደሮች ማሳቸውን በአዝመራ ለመሸፈን እያከናወኑ መሆኑን በመግለፅ እየዘነበ ያለውን ዝናብ ወደ ማሳ የማስገባት ስራ በስፋት እየተካሄደ ነው ብለዋል።
በመጪው ክረምት ከ800 ሺህ በላይ ሄክታር መሬትን በተለያዩ አዝርእቶች በመሸፈን 24 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ቢሮ ኃላፊው አብራርተዋል።
በ2016/17 የምርት ዘመን ከክልሉ 13 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ቢሮው መግለፁ ይታወሳል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026