
መቀሌ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡- በትግራይ ክልል በ2017/18 የምርት ዘመን የተሻለ ምርት ማግኘት የሚያስችሉ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮ ኃላፊው እያሱ አብርሃ(ዶ/ር) እንደገለፁት፤ እየተካሄዱ ካሉ የዝግጅት ስራዎች መካከል እርጥበትን ማከማቸት የሚያስችለው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አንዱ ነው።
የዝናብ ውሃን ወደ ከርሰ ምድር በማስረግ የእርሻ መሬት እርጥበትን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀው በተለይም ከሚቀጥለው መጋቢት ወር ጀምሮ በማሳ ላይ ትኩረት በማድረግ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው በስፋት ይከናወናል ብለዋል።

እንዲሁም ለመጪው ክረምት የሚያስፈልግ አንድ ሚሊዮን ኩንታል ዘመናዊ የአፈር ማዳበሪያ ከወዲሁ እየተጓጓዘ መሆኑን አመልክተዋል።
በክልሉ ለምርት ዘመኑ 150 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር እንደሚያስፈልግ የገለጹት የቢሮ ኃላፊው ባለፈው ዓመት የክልሉ አርሶ አደር በራሱ አቅም 55 ሺህ ኩንታል እንዲያባዛ በመደረጉ እጥረቱን እንደሚያቃልለው አብራርተዋል።
በልግ አብቃይ ከሆኑ ወረዳዎች በተጨማሪ አርሶ አደሮች ማሳቸውን በአዝመራ ለመሸፈን እያከናወኑ መሆኑን በመግለፅ እየዘነበ ያለውን ዝናብ ወደ ማሳ የማስገባት ስራ በስፋት እየተካሄደ ነው ብለዋል።
በመጪው ክረምት ከ800 ሺህ በላይ ሄክታር መሬትን በተለያዩ አዝርእቶች በመሸፈን 24 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ቢሮ ኃላፊው አብራርተዋል።
በ2016/17 የምርት ዘመን ከክልሉ 13 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ቢሮው መግለፁ ይታወሳል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026