የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ለማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ መሳካት የንግድ ከባቢ ሁኔታ መሻሻል ወሳኝነት አለው</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ለማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ መሳካት እና የሀገሪቱን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የንግድ ከባቢ ሁኔታ መሻሻል ወሳኝነት እንዳለው የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለፀ።

ሁለተኛው የንግድ ከባቢ ሁኔታ ምቹነት የሪፎርም ማስጀመሪያ መርኃ ግብር ዛሬ ተካሄዷል።


በዚሁ ወቅት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል የኢትዮጵያን ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ለማፋጠንና ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ መንግስት ከምንጊዜውም በላይ የግሉን ዘርፍ ያሳተፉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

መንግስት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም ስራ ፈጣሪዎች በኢኮኖሚው ዘርፍ የላቀ ተሳትፎ የሚያደርጉበትን ምቹ መደላድል ለመፍጠር የሚያስችል ተግባር እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ለግሉ ዘርፍ ተዋናዮች ቀልጣፋ እና ዘመናዊ አገልግሎት የሚያገኙበትን ሁኔታ በመፍጠር ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ ማገዝ አለብን ብለዋል።

ሚኒስቴሩ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚሰማሩ ባለሀብቶችን ውጤታማነት ለማሳደግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

በዚህም በዛሬው እለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለግሉ ዘርፍ ምቹ የስራ ከባቢን ለመፍጠር ሁለተኛው የንግድ ከባቢ ሁኔታ ምቹነት ሪፎርም መርኃ ግብር በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡

በመርኃ ግብሩ ውጤታማነቱን ለማሳለጥ የሚያስችል ምክክር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መደረጉን ተናግረዋል።

ሁለተኛው ሪፎርም የግሉ ዘርፍ አንቀሳቃሾች ከፖሊሲ አኳያና ከመሰረተ ልማት ጋር በተያያዘ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠትና ኢንቨትመንትን ለማሳደግ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰዋል።

ለግሉ ዘርፍ ምቹ ከባቢን ለመፍጠር የሚደረጉ ማሻሻያዎች በዋናነት እንደ ሀገር የጀመርናቸውን ሪፎርሞች ለማሳለጥ ያስችላሉ ብለዋል፡፡

በአጠቃላይ ማሻሻያዎቹ የሀገሪቱን የንግድ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ 62 ኢኒሼቲቮች የተለዩበት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ኢንሼቲቮች ተጨማሪ የስራ እድል ለመፍጠር፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብና የኢንተርፕራይዞችን ቁጥር ለመጨመር ያስችላሉ ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

ኢንሼቲቮቹ ባለሃብቶች በስራቸው የሚያስፈልጓቸውን ጉዳዮች በተቀላጠፈ መንገድ ለመጨረስ አቅም ይፈጥራሉ ሲሉም አክለዋል።

ኢንሼቲቮቹ ከንግድ ፣ከግብር ፣ከገቢዎች ፣ ከመሰረተ ልማት ፣ከአገልግሎት አሰጣጥ ፣ከዋስትና ፣ከስራ ደህንነት ፣ ከፋይናንስ አቅርቦት ጋር የተያያዙ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የምክክሩ ተሳታፊዎች የግሉን ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለማጎልበት የሚያግዙ ተግባራትን በተናበበና በተቀናጀ መልኩ መስራት አለብን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025