
ባሕር ዳር፤ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብርና ምርት አምራችና አስመራች ግንኙነት አዋጅ የግብርና ምርታማነትን የሚጨመርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተገለፀ።
የግብርና ምርት አምራችና አስመራች ግንኙነትን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ስልጠና በባህር ዳር ከተማ እየተሰጠ ነው።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አጀበ ስንሻው እንዳሉት የአምራቶችና አስመራቾች መስተጋብር ለግብርና ምርታማነት ዕድገት ይበጃል።
አዋጁ አምራቹ የሰብል ግብዓት፣ ቴክኖሎጂና ስልጠና ከአስመራች እንዲያገኝ ብሎም ምርቱን በቀጥታ ለአስመራች እንዲያስረክብ ያግዘዋል ብለዋል።
አስመራች ደግሞ ያስመረተውን ምርት በቀጥታ ተቀብሎ ለኢንዱስትሪም ሆነ ለውጭ ገበያ እንዲያቀርብ ዕድል ይሰጠዋል ነው ያሉት።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር አስተዋጽዖ ያላቸው ሁለት ረቂቅ አዋጆችን አጸደቀ
በዚህም አዋጁ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ሁለቱን ወገን ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ ለትግበራው በጋራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽም፤ አዋጁ አምራቾችና አስመራቾች ውል ገብተው ለጋራ ተጠቃሚነትን የሚሰሩበትና ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አሻራቸውን እንዲያሳርፉ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።

የክልሉ ህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ባለስልጣን የግብዓትና ግብይት ዳይሬክተር አቶ አለምዘውድ ስሜነህ በበኩላቸው አዋጁ ጥራትና ብዛት ያለው ምርት ለማምረት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
በግብርናው ዘርፍ አምራችና አስመራች ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኙ የሚያስችል አዋጅ ተግባራዊ ሊደረግ ነው
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ከክልል እስከ ወረዳ ባለው መዋቅር የባለድርሻ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025