
ባሕር ዳር፤ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብርና ምርት አምራችና አስመራች ግንኙነት አዋጅ የግብርና ምርታማነትን የሚጨመርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተገለፀ።
የግብርና ምርት አምራችና አስመራች ግንኙነትን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ስልጠና በባህር ዳር ከተማ እየተሰጠ ነው።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አጀበ ስንሻው እንዳሉት የአምራቶችና አስመራቾች መስተጋብር ለግብርና ምርታማነት ዕድገት ይበጃል።
አዋጁ አምራቹ የሰብል ግብዓት፣ ቴክኖሎጂና ስልጠና ከአስመራች እንዲያገኝ ብሎም ምርቱን በቀጥታ ለአስመራች እንዲያስረክብ ያግዘዋል ብለዋል።
አስመራች ደግሞ ያስመረተውን ምርት በቀጥታ ተቀብሎ ለኢንዱስትሪም ሆነ ለውጭ ገበያ እንዲያቀርብ ዕድል ይሰጠዋል ነው ያሉት።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር አስተዋጽዖ ያላቸው ሁለት ረቂቅ አዋጆችን አጸደቀ
በዚህም አዋጁ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ሁለቱን ወገን ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ ለትግበራው በጋራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽም፤ አዋጁ አምራቾችና አስመራቾች ውል ገብተው ለጋራ ተጠቃሚነትን የሚሰሩበትና ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አሻራቸውን እንዲያሳርፉ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።

የክልሉ ህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ባለስልጣን የግብዓትና ግብይት ዳይሬክተር አቶ አለምዘውድ ስሜነህ በበኩላቸው አዋጁ ጥራትና ብዛት ያለው ምርት ለማምረት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
በግብርናው ዘርፍ አምራችና አስመራች ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኙ የሚያስችል አዋጅ ተግባራዊ ሊደረግ ነው
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ከክልል እስከ ወረዳ ባለው መዋቅር የባለድርሻ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026