
ባህርዳር፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በግንባታ ኢንዱስትሪው ዘርፍ ዘመን ተሻጋሪ አሻራዎቹን ለማሳረፍ ይበልጥ መዘጋጀት እንዳለበት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተሞች ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አሕመዲን መሀመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
የአማራ ሕንጻ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ስያሜውን ወደ "ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን" በመቀየር የአደረጃጀትና የንግድ ትውውቅ መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተካሂዷል።

በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተሞች ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊና የኮርፖሬሽኑ ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አሕመዲን መሀመድ(ዶ/ር)፤ ኮርፖሬሽኑ በግንባታ ኢንዱስትሪው ዘመን ተሻጋሪ አሻራዎቹን ለማሳረፍ የላቀ ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
የመፈጸምና የተወዳዳሪነት አቅሙን በማሳደግም ትልቅ ራዕይ አንግቦ መነሳቱን ጠቁመው፤ ለተግባራዊነቱ የስራ አመራር ቦርዱ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
በመሆኑም ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በግንባታ ኢንዱስትሪው ዘርፍ ዘመን ተሻጋሪ አሻራዎቹን ለማሳረፍ ይበልጥ መዘጋጀት ይኖርበታል ነው ያሉት።

የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ኮርፖሬሽኑ የገበያ ክፍተትን በመሙላት ከክልሉ አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተልዕኮውን በአግባቡ እየፈፀመ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ከፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ተነስቶ እዚህ ደረጃ እንዲደርስ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ አመስግነው፤ በቀጣይም ለተሻለ እድገትና ስኬት እንዲበቃ እገዛ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
የአደረጃጀትና የስም እንዲሁም የምልክት(ሎጎ) ለውጥ ማድረጉም ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት መፈፀም የሚያስችለው መሆኑን አንስተዋል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ግርማ፤ ኮርፖሬሽኑ በተለይም በህንጻ፣ በአስፋልትና በጠጠር መንገዶች ግንባታ በብቃት በማከናወን የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
የአደረጃጀት፣ የስያሜና የምልክት ለውጥ ማድረጉም እሴቶችን በማጠናከር ተወዳዳሪነትና የገበያ አድማሱን ለማስፋት የሚያግዘው ይሆናል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026