
ዲላ፤የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦የተሻለ ምርት የሚሰጡ የቡና ዝርያዎችን በማልማት ተጠቃሚነታውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።
በክልሉ ዘንድሮ ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ አዲስና ነባር መሬት በቡና ለመሸፈን የችግኝ ማፍላት እንዲሁም የችግኝና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑም ተመላክቷል።
አርሶ አደሮቹ በሽታን ተቋቁመው የተሻለ ምርት የሚሰጡ የቡና ዝርያዎችን እያለሙ መሆኑን ተናግረዋል።
ለዚህም የተፈጥሮ ማዳበሪያና የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራዎች ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
ከአርሶ አደሮቹ መካከል በጌዴኦ ዞን የወናጎ ወረዳ አርሶ አደር ቤቹ አራርሶ፥ በተያዘው ዓመት በዘመናዊ የግብርና አሰራር የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለማልማት የጉድጓድ ቁፋሮና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቃቸውን አንስተዋል።
በኩታ ገጠም አንድ ሄክታር ማሳቸው ቡና በማልማት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ጠንክረው እየሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል።
ቀደም ሲል ቡናን በተለመደው መንገድ ማልማታችን የልፋታችንን ያህል ተጠቃሚ አላደረገንም ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ አርሶ አደር ዘርፌ ባሪ ናቸው።
በተለይም ያረጁ ቡናዎች ምርታማነታቸውን እየቀነሱ በመሆኑ በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በመተካት ልማቱን በማጠናከር ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ለቡና ተከላ የሚሆን የጉድጓድ ቁፋሮና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ሥራ ማከናወናቸውንም ጠቁመዋል።
ከዚህ ቀደም ለቡና ልማት የተፈጥሮ ማዳበሪያ የመጠቀም ልማድ አነስተኛ እንደነበር ያነሱት ደግሞ በዞኑ የዲላ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ዳዊት ጅክሶ ናቸው።
በተያዘው ዓመትም ቡናን በመስመር ለማልማት የጉድጓድ ቁፋሮ ከማከናወናቸው ባለፈ ከቡና ተረፈ ምርት፣ ከፍግና ከተለያዩ ብስባሾች የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል ብሩ በበኩላቸው፣በክልሉ በአማካይ በሄክታር የሚገኘውን 7 ኩንታል የቡና ምርት በቀጣይ ዓመት ወደ 9 ኩንታል ከፍ ለማድረግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ ነው።
ለዚህም የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በዘመናዊ መንገድ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በተያዘው ዓመት ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ልማት ለመሸፈን የጉድጓድ፣የችግኝ ማፍላትና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል።
ለዚህም ለተዘጋጁ ከ32 ሚሊዮን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች እንክብካቤ ከማድረግ ባለፈ ለቡና ልማት የሚውል ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ቶን በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ሥራ ተጠናቋል ብለዋል።
በተጨማሪም አርሶ አደሩን በኩታ ገጠም በማደራጀት ለቀጣይ ተከላ የሚሆን ከ22 ሚሊዮን በላይ ጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ መከናወኑን አመልክተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025