
ዲላ፤የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦የተሻለ ምርት የሚሰጡ የቡና ዝርያዎችን በማልማት ተጠቃሚነታውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።
በክልሉ ዘንድሮ ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ አዲስና ነባር መሬት በቡና ለመሸፈን የችግኝ ማፍላት እንዲሁም የችግኝና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑም ተመላክቷል።
አርሶ አደሮቹ በሽታን ተቋቁመው የተሻለ ምርት የሚሰጡ የቡና ዝርያዎችን እያለሙ መሆኑን ተናግረዋል።
ለዚህም የተፈጥሮ ማዳበሪያና የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራዎች ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
ከአርሶ አደሮቹ መካከል በጌዴኦ ዞን የወናጎ ወረዳ አርሶ አደር ቤቹ አራርሶ፥ በተያዘው ዓመት በዘመናዊ የግብርና አሰራር የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለማልማት የጉድጓድ ቁፋሮና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቃቸውን አንስተዋል።
በኩታ ገጠም አንድ ሄክታር ማሳቸው ቡና በማልማት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ጠንክረው እየሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል።
ቀደም ሲል ቡናን በተለመደው መንገድ ማልማታችን የልፋታችንን ያህል ተጠቃሚ አላደረገንም ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ አርሶ አደር ዘርፌ ባሪ ናቸው።
በተለይም ያረጁ ቡናዎች ምርታማነታቸውን እየቀነሱ በመሆኑ በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በመተካት ልማቱን በማጠናከር ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ለቡና ተከላ የሚሆን የጉድጓድ ቁፋሮና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ሥራ ማከናወናቸውንም ጠቁመዋል።
ከዚህ ቀደም ለቡና ልማት የተፈጥሮ ማዳበሪያ የመጠቀም ልማድ አነስተኛ እንደነበር ያነሱት ደግሞ በዞኑ የዲላ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ዳዊት ጅክሶ ናቸው።
በተያዘው ዓመትም ቡናን በመስመር ለማልማት የጉድጓድ ቁፋሮ ከማከናወናቸው ባለፈ ከቡና ተረፈ ምርት፣ ከፍግና ከተለያዩ ብስባሾች የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል ብሩ በበኩላቸው፣በክልሉ በአማካይ በሄክታር የሚገኘውን 7 ኩንታል የቡና ምርት በቀጣይ ዓመት ወደ 9 ኩንታል ከፍ ለማድረግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ ነው።
ለዚህም የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በዘመናዊ መንገድ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በተያዘው ዓመት ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ልማት ለመሸፈን የጉድጓድ፣የችግኝ ማፍላትና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል።
ለዚህም ለተዘጋጁ ከ32 ሚሊዮን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች እንክብካቤ ከማድረግ ባለፈ ለቡና ልማት የሚውል ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ቶን በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ሥራ ተጠናቋል ብለዋል።
በተጨማሪም አርሶ አደሩን በኩታ ገጠም በማደራጀት ለቀጣይ ተከላ የሚሆን ከ22 ሚሊዮን በላይ ጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ መከናወኑን አመልክተዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026