
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- የኮሪያ ሪፐብሊክ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በመጠቀም መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በኮሪያ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጥሪ አቀረቡ።
የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድል የሚያስተዋውቅ የኢንቨስትመንት ፎረም በኮሪያ ሪፐብሊክ ሴዑል ተካሄዷል።
በፎረሙ ላይ ከ200 በላይ የሚሆኑ የካምፓኒ ባለቤቶች እና ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
በኮሪያ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሴ ዳልኬ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ የተሻለ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ማበረታቻዎች ያላት ሀገር ናት ያሉት አምባሳደሩ ባለሃብቶቹ ይህን እድል በመጠቀም በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታን ለመፍጠር በኢትዮጵያ መንግስት የተደረጉ የቢዝነስ ፖሊሲ ማሻሻያች፣ ዋና ዋና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች እና ምቹ የንግድ ከባቢያዊ ሁኔታዎች የተመለከቱ ጉዳዮች በፎረሙ ላይ ቀርበዋል።
በጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ በኢትዮጵያ የተሰማራው የሺንቴስ ኩባንያ ተሞክሮውን ለባለሃብቶቹ አቅርቧል።
ባለሀብቶቹ ከተደረገው ገለጻ ኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጮች ያላት አገር እንደሆነች ለመገንዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል።
በቀጣይ በኢትዮጵያ የቅድመ-ኢንቨስትመንት ጉብኝት ለማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን በሴዑል የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026