የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>የኮሪያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ዘርፍ እንዲሰማሩ ተጠየቀ</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- የኮሪያ ሪፐብሊክ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በመጠቀም መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በኮሪያ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጥሪ አቀረቡ።

የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድል የሚያስተዋውቅ የኢንቨስትመንት ፎረም በኮሪያ ሪፐብሊክ ሴዑል ተካሄዷል።

በፎረሙ ላይ ከ200 በላይ የሚሆኑ የካምፓኒ ባለቤቶች እና ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

በኮሪያ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሴ ዳልኬ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ የተሻለ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ማበረታቻዎች ያላት ሀገር ናት ያሉት አምባሳደሩ ባለሃብቶቹ ይህን እድል በመጠቀም በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።

ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታን ለመፍጠር በኢትዮጵያ መንግስት የተደረጉ የቢዝነስ ፖሊሲ ማሻሻያች፣ ዋና ዋና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች እና ምቹ የንግድ ከባቢያዊ ሁኔታዎች የተመለከቱ ጉዳዮች በፎረሙ ላይ ቀርበዋል።

በጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ በኢትዮጵያ የተሰማራው የሺንቴስ ኩባንያ ተሞክሮውን ለባለሃብቶቹ አቅርቧል።

ባለሀብቶቹ ከተደረገው ገለጻ ኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጮች ያላት አገር እንደሆነች ለመገንዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይ በኢትዮጵያ የቅድመ-ኢንቨስትመንት ጉብኝት ለማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን በሴዑል የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.