
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- የኮሪያ ሪፐብሊክ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በመጠቀም መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በኮሪያ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጥሪ አቀረቡ።
የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድል የሚያስተዋውቅ የኢንቨስትመንት ፎረም በኮሪያ ሪፐብሊክ ሴዑል ተካሄዷል።
በፎረሙ ላይ ከ200 በላይ የሚሆኑ የካምፓኒ ባለቤቶች እና ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
በኮሪያ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሴ ዳልኬ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ የተሻለ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ማበረታቻዎች ያላት ሀገር ናት ያሉት አምባሳደሩ ባለሃብቶቹ ይህን እድል በመጠቀም በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታን ለመፍጠር በኢትዮጵያ መንግስት የተደረጉ የቢዝነስ ፖሊሲ ማሻሻያች፣ ዋና ዋና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች እና ምቹ የንግድ ከባቢያዊ ሁኔታዎች የተመለከቱ ጉዳዮች በፎረሙ ላይ ቀርበዋል።
በጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ በኢትዮጵያ የተሰማራው የሺንቴስ ኩባንያ ተሞክሮውን ለባለሃብቶቹ አቅርቧል።
ባለሀብቶቹ ከተደረገው ገለጻ ኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጮች ያላት አገር እንደሆነች ለመገንዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል።
በቀጣይ በኢትዮጵያ የቅድመ-ኢንቨስትመንት ጉብኝት ለማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን በሴዑል የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026