
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- በ2018 ዓ.ም በትምህርት ቤቶች የፋይዳ እና የልደት ምዝገባን ቅድመ ሁኔታ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ጀምሮ ያለው የፋይዳ ምዝገባ አፈፃፀም ግምገማ እና የቀጣይ የተማሪዎች ምዝገባ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የዜጎችን መረጃ በማደራጀት በአንድ ቋት መያዝ ከሚያስችሉ አሰራሮች መካከል የፋይዳ እና የልደት ምዝገባዎች ተጠቃሾች ናቸው።
በአሁኑ ወቅትም የፋይዳ ምዝገባ በትምህርት ቤቶች ጭምር በንቅናቄ ለማካሔድ ስራ መጀመሩን አመላክተዋል፡፡
በ2018 ዓ.ም በትምህርት ቤቶች የፋይዳ እና የልደት ምዝገባ ለልዩ ልዩ አገልግሎቶች ቅድመ ሁኔታ እንደሚሆን አመላክተዋል፡፡
በትምህርት ቤቶች ፋይዳ መታወቂያ እንደ ስኮላርሽፕ፣ ምገባ፣ የትራንስፖርት ሰርቪስ እና የመሳሰሉ አገልግሎቶችን ለማግኘት እንደሚረዳ ተናግረዋል።
ምዝገባውን እስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ ለማጠናቀቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዮዳሄ አርዓያስላሴ በበኩላቸው፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ የፋይዳ ምዝገባ ከተጀመረ ወዲህ በርካታ ዜጎችን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
ባለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ወደ 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች ለፋይዳ መታወቂያ መመዝገባቸውን አመላክተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ(ዶ/ር)፣ በመዲናዋ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ሊያስተሳር የሚችል የኢ-ስኩል ሶፍትዌር ለመጀመር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ዛሬ በይፋ የተጀመረው የተማሪዎች የፋይዳ ንቅናቄ የኢ-ስኩል አሰራር በተገቢው መንገድ ለመተግበር ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ በበኩላቸው የትምህርት ቤቶች የፋይዳ ምዝገባ በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን ይሰራል ብለዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አለማየሁ እጅጉ፤ ንቅናቄው በውጤት እንዲጠናቀቅ የግንዛቤ ፈጠራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡
በንቅናቄው ወቅት ለሚያጋጥሙ ችግሮች ፈጥኖ ምላሽ ለመስጠት በየጊዜው መረጃ መለዋወጥ እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025