
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- በ2018 ዓ.ም በትምህርት ቤቶች የፋይዳ እና የልደት ምዝገባን ቅድመ ሁኔታ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ጀምሮ ያለው የፋይዳ ምዝገባ አፈፃፀም ግምገማ እና የቀጣይ የተማሪዎች ምዝገባ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የዜጎችን መረጃ በማደራጀት በአንድ ቋት መያዝ ከሚያስችሉ አሰራሮች መካከል የፋይዳ እና የልደት ምዝገባዎች ተጠቃሾች ናቸው።
በአሁኑ ወቅትም የፋይዳ ምዝገባ በትምህርት ቤቶች ጭምር በንቅናቄ ለማካሔድ ስራ መጀመሩን አመላክተዋል፡፡
በ2018 ዓ.ም በትምህርት ቤቶች የፋይዳ እና የልደት ምዝገባ ለልዩ ልዩ አገልግሎቶች ቅድመ ሁኔታ እንደሚሆን አመላክተዋል፡፡
በትምህርት ቤቶች ፋይዳ መታወቂያ እንደ ስኮላርሽፕ፣ ምገባ፣ የትራንስፖርት ሰርቪስ እና የመሳሰሉ አገልግሎቶችን ለማግኘት እንደሚረዳ ተናግረዋል።
ምዝገባውን እስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ ለማጠናቀቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዮዳሄ አርዓያስላሴ በበኩላቸው፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ የፋይዳ ምዝገባ ከተጀመረ ወዲህ በርካታ ዜጎችን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
ባለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ወደ 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች ለፋይዳ መታወቂያ መመዝገባቸውን አመላክተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ(ዶ/ር)፣ በመዲናዋ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ሊያስተሳር የሚችል የኢ-ስኩል ሶፍትዌር ለመጀመር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ዛሬ በይፋ የተጀመረው የተማሪዎች የፋይዳ ንቅናቄ የኢ-ስኩል አሰራር በተገቢው መንገድ ለመተግበር ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ በበኩላቸው የትምህርት ቤቶች የፋይዳ ምዝገባ በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን ይሰራል ብለዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አለማየሁ እጅጉ፤ ንቅናቄው በውጤት እንዲጠናቀቅ የግንዛቤ ፈጠራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡
በንቅናቄው ወቅት ለሚያጋጥሙ ችግሮች ፈጥኖ ምላሽ ለመስጠት በየጊዜው መረጃ መለዋወጥ እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026