
አርባምንጭ፤የካቲት 23/2017ኢዜአ)፦የአድዋን ድል ጀግንነት በድህነት ላይ በመድገም አገራዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ።
129ኛው የአድዋ ድል በዓል በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በፓናል ውይይት እየተከበረ ነው።
በፓናል ውይይቱ ላይም የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳይ ምክትል ፕሬዚዳንትና የፕሬዚዳንቱ ተወካይ ኢንጂነር ቦጋለ ገብረማሪያም (ዶ/ር)፥ የጥንት አባቶቻችን በማበር የተቀዳጁት የአድዋ ድል ለጥቁር ህዝቦች ነፃነትን ማረጋገጡን አውስተዋል።
የአሁኑ ትውልድም የአድዋን ድል ጀግንነት በድህነት ላይ በመድገም አገራዊ ብልጽግናን ሊያረጋግጥ ይገባል ብለዋል።
በአባይ ወንዝ ጉዳይ ሀጋራዊ የጋራ ትርክት መገንባቱን ጠቅሰው፥ አንድነታችንን ይበልጥ በማጠናከር ድህነት ላይ ድል መቀዳጀት ይጠበቅብናል ሲሉ አመልክተዋል።
ከተባበርን የሀገር ሉዐላዊነትን ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ ሉዐላዊነትን ማረጋገጥ እንደምንችል አድዋ ማሳያችን ነው ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ታሪክ እየዘከርን ታሪክ በመፃፍ ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር የማውረስ ታሪካዊ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።
ከአድዋ ድል አንድነት፣ቆራጥነትና ሀገር ወዳድነትን ልንማር ይገባል ያሉት ደግሞ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተክሉ ወጋየሁ ናቸው።
ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን በመተው ችግሮቻችንን በውይይትና በምክክር መፍታት አለብን ሲሉም አክለዋል።
የጋሞ እና ጎፋ ዞኖች ጥንታዊ ኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር ሊቀመንበር አቶ ተስፋዬ ገመዳ በበኩላቸው፥ የአድዋ ድል የህብርና የአንድነት ውጤት ነው ብለዋል።
ቀደምት አባቶቻችን ዘር፣ብሔር ፥የሃይማኖት ልዩነት ሳያግዳቸው ደማቸውን አፍሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው ኢትዮጵያን አኑረዋል ነው ያሉት።
ኢትዮጵያን ከነ ሙሉ ክብሯ ለመጪው ትውልድ የማስተላለፍ አደራ አለብን ሲሉም አመልክተዋል።
በፓናል ውይይቱም "በኢትዮጵያ ሴቶች የጀግንነት ውሎ እና በዝክረ አድዋ አላማ" ላይ ያተኮሩ ሁለት ሰነዶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል።
በበዓሉ ላይም የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ፣ ጥንታዊት አርበኞች፣የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025