የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ በኢኮኖሚያዊ ትብብራቸው ዙሪያ ተወያዩ</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፡- በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሀኑ ጸጋዬ ከጅቡቲ በጀት ሚኒስትር ኢስማን ኢብራሂም ሮብሌ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም በጅቡቲ ለሚገኙ የኢትዮጵያ ተቋማት የተሻለ የንግድ ሁኔታን መፍጠር የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።

በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ናሽናል ኦይል ኩባንያ(NOC) ሁለቱን ሀገራት በማስተሳሰር እና ንግድን በማሳለጥ ረገድ ትልቅ ሚና ያላቸው ተቋማት መሆናቸው ተነስቷል።

በዚህ ረገድም የተቋማቱን የትብብር ስራዎች ማጠናከር እንደሚገባ ተመላክቷል።

የተቋማቱን ሂደት በመከታተል የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማጎልበት በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.