
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ)፡- 100 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 2 በመቶ መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።
የፕሮጀክቱ ግንባታ በታህሳስ ወር 2013 ዓ.ም ከዴንማርክ መንግሥት በተገኘ ብድር እና ዕርዳታ ከ146 ሚሊዮን ዩሮ በላይ በጀት ተጀምሯል።
የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈቃዱ አብርሃም ኃይል ማመንጫው እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 46 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 የንፋስ ተርባይኖች አሉት።
የ22 ተርባይኖች ተከላ መጠናቀቁንና የ20ዎቹ ተርባይኖች የቅድመ ፍተሻ ሥራ መከናወኑን አመልክተዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማመንጫው የባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ሥራ ከ95 በመቶ በላይ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ ከ60 በመቶ ደርሷል።
እያንዳንዱን ተርባይን የሚያገናኙ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በሥራ ተቋራጩ ምክንያት መዘግየት አፈጻጸሙም 54 በመቶ ላይ እንደሚገኝና አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 78 ነጥብ 2 መድረሱን አመልክተዋል።
የግንባታው ሥራ ተቋራጭ ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒዌብል ኢነርጂ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ኤድዋርዶ ጎንዛሌዝ አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም መልካም በሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ቀሪ ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን መግለጻቸውን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026