የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ 78 በመቶ ደርሷል</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ)፡- 100 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 2 በመቶ መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።

የፕሮጀክቱ ግንባታ በታህሳስ ወር 2013 ዓ.ም ከዴንማርክ መንግሥት በተገኘ ብድር እና ዕርዳታ ከ146 ሚሊዮን ዩሮ በላይ በጀት ተጀምሯል።

የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈቃዱ አብርሃም ኃይል ማመንጫው እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 46 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 የንፋስ ተርባይኖች አሉት።

የ22 ተርባይኖች ተከላ መጠናቀቁንና የ20ዎቹ ተርባይኖች የቅድመ ፍተሻ ሥራ መከናወኑን አመልክተዋል።

እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማመንጫው የባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ሥራ ከ95 በመቶ በላይ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ ከ60 በመቶ ደርሷል።

እያንዳንዱን ተርባይን የሚያገናኙ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በሥራ ተቋራጩ ምክንያት መዘግየት አፈጻጸሙም 54 በመቶ ላይ እንደሚገኝና አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 78 ነጥብ 2 መድረሱን አመልክተዋል።

የግንባታው ሥራ ተቋራጭ ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒዌብል ኢነርጂ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ኤድዋርዶ ጎንዛሌዝ አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም መልካም በሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ቀሪ ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን መግለጻቸውን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.