የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ማዕከሉ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ተጨማሪ አቅም ይሆናል- የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለኢትዮጵያ ተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅም መሆን በሚያስችል መልኩ የተገነባ መሆኑን የተፎካካሪ ፓርቲ እና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የሲቪል ማህብረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች የአዲስ አፍሪካ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል።


የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የፋይናንስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክፍለ ማርያም ሙሉጌታ፤ ማዕከሉ መዲናዋን ውብ ገጽታ የማላበስ አካል መሆኑን ገልጸዋል።

የመዲናዋን ግዙፍ ፕሮጀክቶች አለማድነቅ ንፉግነት ነው ያሉት አቶ ክፍለ ማርያም፤ ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጥ የሚረጋገጠው በብርቱ ስራና በትብብር መርህ ነው ብለዋል።

ለማዕከሉ ግንባታ ሂደት ሚና የነበራቸውን አካላትም አመስግነዋል።


የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የአደረጃጀትና የአቅም ግንባታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙባረክ ረሽድ፤ በዲፕሎማቲክ መዲናዋ የተገነባው ማዕከሉ ዓለም አቀፍ ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን በመጥቀስ አድንቀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማና የፌደራል ዕድሮች ምክር ቤት ሰብሳቢ ታምራት ገብረ-ማርያም፤ የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።


ማዕከሉ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የንግድ ትርዒትና ባዛር ሁነቶችን ማስተናገድ አቅም እንዳለው በምልከታቸው እንዳረጋገጡ ተናግረዋል።

የአዲስ ትውልድ ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ቤዛ ተሰማ፤ ማዕከሉ የኢትዮጵያን አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማጉላት የሚያስችል አቅም እንዳለው መታዘባቸውን ገልጸዋል።


የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች እንዳሉት ማዕከሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂና ተያያዥ መሰረታዊ ግብዓቶችን በማሟላት ምርትና አገልግሎቶችን በብቃት ማስተናገድ በሚያስችል መልኩ ተገንብቷል።

ማዕከሉ በኢትዮጵያ የነበረውን ደረጃውን የጠበቀ የንግድ ኤግዚቢሽንና ባዛር ማስተናገጃ ስፍራ ጥያቄ በመፍታት ለሀገር ኢኮኖሚ ሌላ አቅም ነው ብለዋል።

በንግድና ኢንቨስትመንት ማህብረሰብ ትስስር በመፍጠር እና ለግብይት መሳለጥ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.