አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለኢትዮጵያ ተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅም መሆን በሚያስችል መልኩ የተገነባ መሆኑን የተፎካካሪ ፓርቲ እና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች ገለጹ።
የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የሲቪል ማህብረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች የአዲስ አፍሪካ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል።
የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የፋይናንስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክፍለ ማርያም ሙሉጌታ፤ ማዕከሉ መዲናዋን ውብ ገጽታ የማላበስ አካል መሆኑን ገልጸዋል።
የመዲናዋን ግዙፍ ፕሮጀክቶች አለማድነቅ ንፉግነት ነው ያሉት አቶ ክፍለ ማርያም፤ ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጥ የሚረጋገጠው በብርቱ ስራና በትብብር መርህ ነው ብለዋል።
ለማዕከሉ ግንባታ ሂደት ሚና የነበራቸውን አካላትም አመስግነዋል።
የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የአደረጃጀትና የአቅም ግንባታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙባረክ ረሽድ፤ በዲፕሎማቲክ መዲናዋ የተገነባው ማዕከሉ ዓለም አቀፍ ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን በመጥቀስ አድንቀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማና የፌደራል ዕድሮች ምክር ቤት ሰብሳቢ ታምራት ገብረ-ማርያም፤ የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።
ማዕከሉ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የንግድ ትርዒትና ባዛር ሁነቶችን ማስተናገድ አቅም እንዳለው በምልከታቸው እንዳረጋገጡ ተናግረዋል።
የአዲስ ትውልድ ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ቤዛ ተሰማ፤ ማዕከሉ የኢትዮጵያን አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማጉላት የሚያስችል አቅም እንዳለው መታዘባቸውን ገልጸዋል።
የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች እንዳሉት ማዕከሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂና ተያያዥ መሰረታዊ ግብዓቶችን በማሟላት ምርትና አገልግሎቶችን በብቃት ማስተናገድ በሚያስችል መልኩ ተገንብቷል።
ማዕከሉ በኢትዮጵያ የነበረውን ደረጃውን የጠበቀ የንግድ ኤግዚቢሽንና ባዛር ማስተናገጃ ስፍራ ጥያቄ በመፍታት ለሀገር ኢኮኖሚ ሌላ አቅም ነው ብለዋል።
በንግድና ኢንቨስትመንት ማህብረሰብ ትስስር በመፍጠር እና ለግብይት መሳለጥ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ነው ያሉት።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025