የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>የገጠር ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት ወደተግባር ተገብቷል</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ)፡-የገጠር ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ዘላቂ የልማት ግቦችን ማሳካት የሚያስችል ፕሮግራም ተነድፎ ወደተግባር መገባቱን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ክልል የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢኒሼቲቪ ትግበራ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሃዋሳ ከተማ ተካሂዷል።


የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር አለባቸው ንጉሴ (ዶ/ር) በዚህ ጊዜ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በገጠር ያለውን ሀብት፣ ጉልበትና እውቀት መሰረት ያደረገ ኢንዱስትሪ ለማስፋፋት የሚያስችል ፕሮግራም ተቀርጾ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡

ፕሮግራሙ በገጠር ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚያስችል ሲሆን ኤክስፖርትንና ተኪ ምርትን በማሳደግ ረገድም ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።

በሲዳማ ክልል ሀዋሳና ይርጋለም አካባቢ ያለውን ሰፊ የኢንዱስትሪ ልምድ በገጠር ወረዳዎች በመተግበር ፕሮግራሙን ማሳካትና የሚፈገለውን ውጤት ማምጣት እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡


የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጎሳዬ ጎዳና በበኩላቸው በገጠር ኢዱስትሪዎችን ለማስፋፋት የተቀረጸውን ሃገራዊ ፕሮግራም መነሻ በማድረግ ክልላዊ ኢንሼቲቪ መቀረጹን ገልጸዋል፡፡

ኢንሼቲቩ በክልሉ ባሉ 30 ወረዳዎች የሚተገበርና የወረዳዎቹን አቅም በመለየት የሚከናወን መሆኑም አስረድተዋል።

በዚህም በየወረዳዎቹ ከሦስት እስከ አምስት አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመፍጠር በበጀት ዓመቱ 104 አዳዲስ የገጠር ኢንዱስትሪዎች ለመገንባት እቅድ ተይዟል ብለዋል፡፡

በክልሉ በተፈጥሮ ሃብትና ግብርና፣ በማዕድንና በእንስሳት ሃብት ልማት ዘርፍ ያለውን የግብዓት አቅም ወደ ኢንዱስትሪ ለመቀየር ትኩረት መሰጠቱንም ተናግረዋል፡፡

በክልሉ 8 ኢንሼቲቮችና 68 ፓኬጆች ተቀርጸው የቤተሰብ ብልጽግና ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ አሸናፊ ኤሊያስ ናቸው፡፡

በክልል ደረጃ ከተቀረጹ የልማት ፓኬጆች መካከል የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንደሚጠቀስ ገልጸው በገጠር ኢንዱስትሪዋችን ለማስፋፋት በየአካባቢው ያለው አቅም ተለይቷል ብለዋል፡፡

በዚህም አመራሩ ሞዴል አርሶ አደሮችን ጨምሮ ጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራትን በመደገፍ አምራች ኢንዱስሪትውን እንዲቀላቀሉ ማገዝ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካካል የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሰለሞን ዮናስ እንደገለጹት የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽንን ለማስፋፋት የተጀመረው ኢንሼቲቭ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡

እንደ ዞን ቡናን ጨምሮ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በሰብልና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ያሉ አቅሞች መለየታቸውን ጠቁመው፣ ማህበራትንና ሞዴል አርሶ አደሮችን ወደ ኢንዱስትሪው ለማስገባት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡

በዚህም በሃገርም ሆነ በክልል ደረጃ ለተቀረጹ ፕሮግራሞች ስኬት በትኩረት እንደሚሰራ ነው ያመለከቱት።

በመድረኩ በሃገርና በክልል ደረጃ የገጠር ኢንዱስትሪላይዜሽንን ለመተግበር በተዘጋጁ ሰነዶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.